ለቆጠራ ካርታ ዝግጅት የGIS እና Advance Remote Sensing ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ሲሰጠ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ

aa3a1597

ግንቦት 25/2017ዓ.ም አዳማ፣

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ለተቋሙ የካርቶግራፊና ጂ አይ ኤስ  ባለሙያዎች በካርታ ማካለል፣ GIS እና Advance Remote Sensing ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ሲሰጠ የቆየው የተግባር ስልጠና ተጠናቀቀ።

aa3a1616

በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አብዱራዛቅ ዑመር  የስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩትና የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ለሀገራችን ልማት ዕቅድና ክትትል ግብዓት የሚሆኑ  የስታቲስቲክስና ጂኦ ስፓሻል መረጃዎች የማቅረብ ሀላፊነት የተሰጣቸው ተቋማት በመሆናቸው በሁለቱም ተቋማት ያለውን ዕውቀትና  ልምድ በተለየዩ አግባቦች ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመው በጋራ በመስራት ላይ እንዲሚገኙ አንስተው ለ15 ቀናት ሲሰጥ ቆይቶ ዛሬ የተጠናቀቀው ስልጠናም የቆጠራ ካርታ ማካለል ስራን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ የGIS እና  Advance Remote Sensing ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ያለውን ዕውቀትና ልምድ በተግባር ለማካፈል የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀው፤ ወደተቋማችሁ  ስትመለሱ ያገኛችሁትን ስልጠና ተግባራዊ ለማድረግ በትጋት መስራት ይኖርባችኋል ሲሉ በስልጠናው ለተሳተፋት ባለሙያዎች  መልዕክት አስተላልፈዋል።

aa3a1584

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስታቲስቲክስ ዲጂታላይዜሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሜሮን ክፈለው በተቋሙ የቆጠራ ካርታ ማካለል ስራ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ የሚታዩ ክፍተቶችን በመለየት ስራውን  በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ የባለሙያዎችን ቴክኖሎጂ የመጠቀም አቅም ለማሻሻል ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀው  በቀጣይም በካርታ ዝግጅት፣ GISቴክኖሎጂና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ተቋሙ ከስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት በጋራ  እንደሚሰራ  ገልፀዋል።

aa3a1589

የስልጠናው ተሳታፊዎችም ለስራቸው ጠቃሚ የሆነ የጽንሰ ሀሳብና የተግባር እውቀት እንዳገኙ ገልፀዋል።

aa3a1587