ሐምሌ 15/11/2018 ዓ.ም ባቱ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየዓመቱ የሚያካሄደው የግብርና ናሙና ጥናት የቅድመ ዝግጅት ተግባራት አካል የሆነው የመረጃ ሰብሳቢዎች አሰልጣኝ ስልጠና በባቱ ከተማ በኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ እየተሰጠ ይገኛል። በስልጠናው መክፈቻ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የተቋሙ ም/ዋ/ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ጀሚላ መሀመድ የ2019 ዓ.ም የግብርና ናሙና ጥናት ለማካሄድ የሚደረጉት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በሀገራችን ሁለተኛ ዙር ግብርና ቆጠራ […]