መስከረም 26/2018ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2017ዓ.ም ባካሄደው የግብርና ቆጠራ የተገኙትን ልምዶች ለናሚቢያ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ የማካፈል የስልጠና መርሀ-ግብር በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት እየሰጠ ይገኛል። በመድረኩ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የግብርና ዘርፍ ስታቲስቲክስ መረጃዎች ከአመታዊ የግብርና ናሙና ጥናት በመሰብሰብ፣ በማጠናቀርና ሪፖርት አዘጋጅቶ ለመንግስትና ለሌሎች […]