ሐምሌ 24/2017ዓ.ም ለገጣፎ፣

የፕላንና ልማት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 700 ሚሊየን የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በሸገር ከተማ በለገዳዲ ለገጣፎ ክፍለ ከተማ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አካሄዱ።

መርሀ ግብሩን በንግግር ያስጀመሩት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ጥሩማር አባተ በሀገራችን የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር መካሄድ ከጀመረበት ጊዜ እስከአሁን ወደ40 ቢሊየን ችግኞች መተከላቸው አንስተው ይህም በአየር ንብረት ለውጥ፣ በግብርናና በኢኮኖሚው ዘርፍ ከፍተኛ ውጤት የተገኘበት መሆኑን የገለፁ ሲሆን በቀጣይም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሩን ቀጣይነት በማረጋገጥ ከተረጂነት ለመውጣትና በምግብ ራስን የመቻል እቅድ ለማሳካት ዛሬ የምንተክለው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው ሲሉ ገልፀዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የሸገር ከተማ የለገዳዲ ለገጣፎ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ም/አስተዳደሪ ወ/ሮ ሰዓዳ እስማኤል በክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻር መርሀ ግብር ተግባርን በማስቀጠል ልመናን ታሪክ እናደርጋለን ሲሉ ገልፀዋል።



በዕለቱ ከአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሩ በተጨማሪ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማት 100 ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።




