የኦዲት አሰራርና መረጃ አያያዝ ላይ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

aa3a8521.jpg 1

ሰኔ14/2017 ዓ.ም አዳማ፣

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የኦዲት አሰራርን አስመልክቶ በተለያዩ ርዕሶች ላይ ከዋናው መስሪያ ቤት እና ከቅርንጫፍ ለተወጣጡ  የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡

aa3a8527.jpg

ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የተቋሙ የዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብነት ሃዋዝ ባደረጉት ንግግር ስልጠናው በኦዲት አሰራርና መረጃ አያያዝ የሰራተኛውን ክህሎት ለማጎልበት፤ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ውሳኔ እንዲሰጡ ባለሙያዎችን ለማብቃት ፤የቴክኖሎጂ  አጠቃቀም ለማሳደግ የተዘጋጀ በመሆኑ ተገቢውን ትኩረት በመስጠት በንቃት በመሳተፍ በስልጠና የምታገኙትን ዕውቅት ተግባር ላይ እንድታውሉ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

aa3a8533.jpg

ስልጠናው ከፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች ለቀጣይ ሁለት ቀናት በተለያዩ ርዕሶች ላይ እንደሚሰጥ  ለማወቅ ተችሏል፡፡

aa3a8535.jpg
aa3a8576.jpg