ለሁለተኛ ዙር የአሰልጣኞች ስልጠና አስተባባሪዎች የስራ መመሪያ ተሰጠ

ነሐሴ 2/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣

1t8a6102

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2018ዓ.ም ለሚካሄደው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በ13 የስልጠና ማዕከላት ከነሐሴ 7/2017ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጠውን የአሰልጣኞች ስልጠና ለማስተባበር ከዋናው መስሪያ ቤት ወደ ማዕከላቱ ለተመደቡት 80 ባለሙያዎች የስራ መመሪያ  ተሰጠ።

1t8a6140

በመድረኩ ላይ የተገኙት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በከር ሻሌ በ2017ዓ.ም በተሰሩት ትላልቅ ሀገራዊ ጥናቶችና ቆጠራ የተገኙትን መልካም ተሞክሮዎች በማስቀጠል እንደክፍተት የታዩትን በማረም ስልጠናው በታቀደው መሰረት ስኬታማ እንዲሆን በከፍተኛ ትጋትና ሀገራዊ ሀላፊነት መስራት እንደሚጠበቅባቸው የስራ መመሪያ ሰጥተዋል።

1t8a6132

ስልጠናው ከነሐሴ 7 እስከ 28/2017ዓ.ም በሁሉም ማዕከላት እንደሚሰጥ ከወጣው መርሀ ግብር ለመረዳት ተችሏል።

1t8a6115
1t8a6122 2