በመካከለኛ ዘመን (2016-2018 ዓ.ም) የስታቲስቲክስ ልማት ፕሮግራም ክንውን አፈፃፀም ላይ ውይይት ተካሄደ

ጥር 17/2018 ዓ.ም አዳማ፣

photo 2026 01 25 18 12 32

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በመካከለኛው ዘመን (2016 2018 ዓ.ም) የስታቲስቲክስ ልማት ስትራቴጂክ ዕቅድ ክንውን ላይ ከተወካዮች የምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላት ጋር በአዳማ ከተማ ውይይት አካሄደ።

photo 2026 01 25 18 12 23 1

በመድረኩ ተገኝተው ስልጠናውን ያስጀመሩት የተከበሩ አቶ ደሳለኝ ወዳጀ ተቋሙ ላለፉት ስድስት አስርት አመታት ለሀገሪቱ ልማት ዕቅድ ፖሊሲና ስትራቴጂ ለማዘጋጀት የሚያስፈልጉትን መረጃዎች በማቅረብ በየዘመኑ በሀገራችን ለተመዘገቡ የልማት ዕድገት የራሱን ደማቅ አሻራ እያበረከተ የሚገኝ አንጋፋ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል፡፡

photo 2026 01 25 18 12 22

የስታቲስቲክስ መረጃ ለሀገራችን ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታና የዜጎች ፍትሀዊ ተጠቃሚኒነት የተረጋገጠበት ሀገር ለመገንባት የማይተካ ሚና እንዳለው ያስረዱት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ በረከት ፍስሀፅዮን መንግስት ይህንን ተረድቶ በሀገሪቱ ጠንካራ የስታቲስቲክስ ተቋም እንዲኖር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

photo 2026 01 25 18 12 33

በተቋሙ በመካከለኛ ዘመን (2016 – 2018 ዓ.ም) የስታቲስቲክስ ልማት ስትራቴጂ የእስከ አሁን አፈጻጸሙ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

photo 2026 01 25 18 12 39

የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በከር ሻሌ የተከበሩ የህዝብ ተወዮች ምክር ቤት ቋሚ አባላትና አመራሮች በተቋማችን እየተሰሩ የሚገኙት ስራዎች ላይ ለመወያየትና ለመደጋፍ ጥሪያችንን አክብሮ በመገኘታቸው ያላቸውን ምስጋና አቅርበው በተከበሩት የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አባላት የተነሱትን ገንቢ ሀሳቦች በመውሰድ በቀጣይ በሚከናወኑ ቀሪ የበጀት ዓመቱ ተግባራት በማካተት ተግባራዊ እንደሚደረጉ ገልጸዋል።

photo 2026 01 25 18 12 24

የውይይት መድረኩን የመሩት በተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ የተከበሩ ወ/ሮ መሠረት ሀይሌ ውይይቱ ስለተቋሙ ያላቸውን ግንዛቤ እንዳሳደገላቸው በማንሳት ተቋሙ ከዚህ በተሻለ ሀገርን የማገልገል አቅም እንዲኖረው የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አባላት አስፈላገውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል፡፡

photo 2026 01 25 18 12 26
photo 2026 01 25 18 12 28
photo 2026 01 25 18 12 30
photo 2026 01 25 18 12 31