ታህሣሥ 21/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

በተቋሙ ዋና መሥሪያ ቤት ለሁለተኛ ጊዜ የዕውቀት ሽግግር መድረክ ተዘጋጅቶ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ ተሠርቷል።

የተቋሙ የስታቲስቲክስ መረጃ ስርጭት እና ተደራሽነት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ትግስት በቀለ በተቋሙ ውስጥ የሚገኙ ሁሉም የሥራ ክፍሎች ማንኛውንም ዕውቀት በአግባቡ መሰነድ እንዳለባቸው አንስተው፣ የዕውቀት ሽግግር የተቋሙ ባህል በማድረግ፣ ዕውቀትን መለዋወጥ እና ለተተኪ ትውልድ በተደራጀ መልኩ ማስተላለፍ የመድረኩ ዋና ዓላማ መሆኑን ገልፀዋል።

በተዘጋጀው መድረክ ላይ በሥነ-ሕዝብ እና ጤና ጥናት፣ የሰው ሀብት አስተዳደር መረጃ አያያዝ እና የICT አጠቃቀም ፖሊሲን በተመለከተ ነባር ዕውቀቶች ላይ ገለጻ ቀርቦ ግንዛቤ የተፈጠረበት ሲሆን የመድረኩ ተሳታፊዎች የእውቀት ግብይት መድረኩ መዘጋጀቱ ለልምድና ለዕውቀት ሽግግር ጠቃሚ መሆኑን ገልጸው መድረኩ ቀጣይነት እንዲኖረው አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

