በግብርና ቆጠራ ላይ ውይይት ተደረገ

ታህሳስ 24/2017ዓ.ም፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2017ዓ.ም እያካሄደ በሚገኘው የግብርና ቆጠራ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የግብርና ቢሮ ጋር ውይይት አደረገ።

በውይይቱ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የኢኮኖሚ ስታቲስቲክስ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ቀሬ የተገኙ ሲሆን ከግብርና ቆጠራ የሚገኘው መረጃ ለሀገር ያለውን ጠቀሜታ በመረዳት የተጀመረውን የግብርና ቆጠራ በጋራ በማሳካት ጥራት ያለውና ተዓማኒ መረጃ ለተጠቃሚው ማቅረብ አለብን ሲሉ ገልፀዋል።

በውይይት መድረኩ የግብርና ቆጠራ ከቅድመ ዝግጅት አሁን እስከደረሰበት ያለውን አፈፃፀም የሚያሳይ ገለፃ በግብርና ስታቲስቲክስ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ አብዱላዚዝ ሽፋ ገለጻ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በመድረኩ የክልሉ ግብርና ቢሮ ሀላፊ እና የስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊዎች ተሳትፈዋል።

472314119 576822531902973 8676117319365456609 n
472521511 576822458569647 3195258541255847300 n
472596252 576822325236327 7434221032104209361 n