በ2018 ዓ.ም ለሚካሄደው የግብርና ናሙና ጥናት የአሰልጣኞች ስልጠና ተጀመረ

1t8a5575.jpg

ሐምሌ 28/2017ዓ.ም አዳማ፣
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየዓመቱ ከሚያካሂዳቸው የናሙና ጥናቶች አንዱ የሆነውን የ2018ዓ.ም ግብርና ናሙና ጥናት የመስክ ስራ የሚሰሩትን መረጃ ሰብሳቢዎች የሚያሰለጥኑ አሰልጣኞች ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።

1t8a5562.jpg
1t8a5605.jpg


በስልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የ2018ዓ.ም የግብርና ናሙና ጥናትን ከሁለተኛ ዙር ሀገር አቀፍ የግብርና ቆጠራ የመስክ ስራ በሚጠናቀቅበት ማግስት ማካሄድ ያስፈለገው በጥናቱ የሁለተኛ ዙር የግብርና ቆጠራ ውጤትን ለመገምገም (validate) ለማድረግ ፣ የግብርና ሴክተር መረጃዎችን ሳይቆራረጡ (Time series) በመጠበቅ በቀጣይነት በማደራጀት ለዘርፉ እቅድና ምርምር ለማዋል፣ ዓመታዊ የሀገሪቱን የእደገት ምጣኔ ለማስላት፣ በምርት ዘመኑ የሚኖረውን የሰብል ምርትና የእንስሳት ሀብት እድገትን በማወቅ ለመንግስት በምርት እጥረትና ትርፍ ምርት በመመረቱ ምክንያት የሚፈጠሩትን ተፅዕኖዎች ለመቀነስ የሚያስችል መረጃ ቀድሞ ለመስጠት ጥናቱን ማካሄድ አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በስልጠናው የሚሳተፉ ሰልጣኞች ዓመቱን በሙሉ ሲካሄድ ከቆየው የሁለተኛ ዙር የግብርና ቆጠራ በተለያየ ደረጃ በነበራችሁ ተሳትፎ የተገኙትን ጠቃሚ ልምዶችና እንደክፍተት የታዩ ጉዳዮችን በስልጠናችሁ ወቅት በመወያየትና ልምድ በማጋራት ቀጣይ በመስክ ስራው ለሚሳተፈው የሰው ሀይል የተሟላ ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል እውቀትና ልምድ ለመጨበጥ ስልጠናውን በትኩረት መሳተፍ እንደሚገባቸው መመሪያ በመስጠት ስልጠናውን አስጀምረዋል።

1t8a5594.jpg
1t8a5600.jpg


የግብርና ስታቲስቲክስ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ አብዱላዚዝ ሽፋ ስለጥናቱ አጠቃላይ ገለፃ በመስጠት ስልጠናው ለሚቀጥሉት 10 ቀናት በጥናቱ ጽንሰ ሀሳብ፣ ስለጥናቱ ስነ ዘዴ፣ መጠይቆችና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ከ26ቱ የተቋሙ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለተውጣጡ ስታቲስቲሺያን እንደሚሰጥ ገልፀዋል።

1t8a5603.jpg
1t8a5611.jpg