ሐምሌ 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በዓለም ባንክ ድጋፍ በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር በገጠር መንገድ ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮጀክት የሚሰሩትን የገጠር መንገድ ግንባታ ስራዎች መሰራታቸውን ለማረጋገጥ (Verification) የሚያስችል ስራ ለመስራት ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር ስምምነት ተፈራረመ።


የስምምነት ሰነዱን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ የትምጌታ አስራት እና የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የተፈራረሙ ሲሆን የተሰጣቸውን ሀላፊነት በጥራትና በታማኝነት በተባለው ጊዜ አጠናቀው ለማስረከብ እንደሚሰሩ ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።

የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በብቁ ባለሙያዎች የተደራጀና የካበት ልምድ ካላቸው የሀገራችን ተቋማት አንዱ መሆኑን አንስተው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በዓለም ባንክ ድጋፍ እየተከናወነ የሚገኘውን የገጠር መንገዶች ተደራሽነት ፕሮጀክት የማረጋገጥ (Verification) ስራውን በጥራትና በብቃት እንደሚወጣ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።

