ከፍተኛ አመራሩ ለክልሉ አመራር የስታቲስቲክስ ልማት ፕሮግራም እንዲሳካ የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበ

1t8a4869.jpg

የሲዳማ ብሔራዊ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ ደስታ ሌዳሞ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በስታቲስቲክስ ልማት ዕቅድ ፕሮግራም እያከናወናቸው በሚገኙ ቆጠራዎችና ጥናቶች ላይ ለስራው መሳካት በሲዳማ ክልል ከሚገኘው የሀዋሳ ስታቲስቲክስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ጋር በቅርበት በመደገፍ ለሀገራዊ ስታቲስቲክስ ቆጠራዎች እና ጥናቶች መሳካት ምቹ ሁኔታዎች እንደሚፈጥሩ ገልፀዋል:: በ2017ዓ.ም በክልሉ ውስጥ የተከናወኑ ተግባራትም ውጤታማ እንደነበሩ እና የክልሉ ድጋፍ አዎንታዊ ድርሻ እንደነበረው የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አመራሮች ገልፀዋል:: ለቀጣይም ይሄው ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አመራሩ ጠይቋል::