ክልሎች በብሔራዊ ስታቲስቲክስ ስርዓት ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያዩ

1t8a4241

ጥቅምት25/2018 ዓ.ም

የፕላንና ልማት ሚኒስትርና የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በጋራ ባዘጋጁት ብሔራዊ ስታቲስቲክስ ስርዓት ረቂቅ አዋጅ ላይ የክልልና የከተማ አስተዳደር የፕላንና ልማት ቢሮ የስራ ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሙያዎች በቢሾፍቱ ከተማ ከጥቅምት 24-25/2018 ዓ.ም ውይይት አደረጉ።

1t8a4250 1

በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ተገኝተው ውይይቱን ያስጀመሩት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ኤቢሳ አሰፋ በየጊዜው እያደገ የመጣውን ሳይንሳዊ የስታቲስቲክስ መረጃ ፍላጎት ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በሚያሳትፈው የብሄራዊ ስታቲስቲክስ ስርዓት ጥላ ስር በተሟላ መልኩ ለመመለስ ከሀገራችንና አለም አቀፍ መሰረታዊ ህጎች ጋር የሚናበብ ብሄራዊ የስታቲስቲክስ ስርዓት የሚመራበት የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀትና ተግባራዊ ማድረግ ለሀገራዊ ስታቲስቲክስ ዘርፍ ልማት ስኬታማነት ከሚያስፈልጉ መሰረታዊ ጉዳዮች አንዱ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

1t8a4267 1

አቶ አብነት ሐዋዝ የዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ የክልልና ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ቢሮ አሁን ለውይይት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በሀሳብ ከማዳበር በተጨማሪ በቀጣይ አዋጁ ተግባራዊ ሲደረግም ያላቸው ድርሻና ተጠቃሚነት የጎላ መሆኑን በመረዳት የተሟላ ሀሳብ በመስጠት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ ማዳበር እንደሚጠበቅባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል ፡፡

1t8a4293
1t8a4313

ተሳታፊዎች የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ለሀገራችን የስታቲስቲክስ ስርዓት ዕድገት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አንስተው ረቂቅ አዋጁ ዳብሮ ስራ ላይ ሲውል ሀገራችን ወጥና ተመጋጋቢ የሆነ የመረጃ ስርዓትና ፍሰት እንዲኖራት ከማስቻል አንጻር የአዋጁ ሚና የጎላ መሆኑን ገልፀዋል።

1t8a4308
1t8a4304

ከ12ቱ ክልሎችና ከሁለቱ ከተማ ፕላንና ልማት ቢሮ የተውጣጡ የቢሮ ሀላፊዎችና ባለሙያዎች በአጠቃላይ 40 ሰዎች በውይይቱ ላይ ተሳትፈዋል።

1t8a4280
1t8a4259