የሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች ፐርሶኔል መረጃ መረጋገጥ የሙከራ ጥናት ላይ ለሚሳተፉ ባለሙያዎች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ

592909118 834367229481834 2095079402501593938 n

ህዳር 22/2018 ዓ.ም አዳማ

የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ እና ኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በጋራ የሚያካሂዱት የሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች ፐርሶኔል መረጃ መረጋገጥ የሙከራ ጥናት(Testing Survey) ላይ ለሚሳተፉ ባለሙያዎች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ።

587478793 834367306148493 4070635545414919317 n

ኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በከር ሻሌ ለመስክ ስራ በዘርፍ ብቃት ባላቸው የተቋሙ ባለሙያዎች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ፤ወደ ስራ ሲገባ በተግባር የበለጠ መዳበር እንዳለባቸው አንስቶ ሰልጣኞች በስልጠና ያገኙት የንድፈሃሳብናየተግባር ዕውቀትን በተገቢ መልኩ በመጠቀምየተሰጣቸውን ኃላፊነት ለመወጣት መስራት እንደሚገባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

592347168 834367599481797 7130450657540354817 n

የስልጠናው መዝጊያ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ለስራው ስኬት እያደረገ ለሚገኘው የተናበበ ቅድመ ዝግጅት ተግባር አመስግነው፣ ሰልጠኞች መረጃ ለሀገርና ለእየንደንዱ ሲቨል ሰርቫት ያለውን ከፍታኛ ጥቅም በመወቅ የተሰጠቸውን ኃላፊነት በትጋት መወጣት አንደሚጠበቅባቸው የስራ መመሪያ በመስጠት ስልጠናው ተጠናቋል።

591930904 834367549481802 915918441860973861 n
589658904 834367269481830 1700009675386247755 n