የቆጠራ ካርታዎችን ወቅታዊ ለማድረግ የሚያግዝ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

ጥር 18/2018 ዓ.ም ቢሾፍቱ፣

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ለኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የሚውሉ ካርታዎች ወቅታዊ ለማድረግ የሚያግዝ ስልጠና ከዋና መስሪያ ቤት፣ ከአዲስ አበባ፣ ከአዳማና ከአምቦ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለተውጣጡ ባለሙያዎች እየሰጠ ይገኛል።

photo 2026 01 26 14 59 38 2

ስልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የተቋሙ የስታቲስቲክስ ዲጂታላይዜሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሜሮን ክፈለው የቆጠራ ካርታ ስራ ለቆጠራዎችና ለጥናቶች መረጃ ለመሰብሰብ ዋነኛና ወሳኝ ግብዓት መሆኑን አንስተው ሰልጣኞች ካርታውን ለመስራት የሚያስችል ዕውቀትና ክህሎት በማግኘት ትክክለኛና ጥራት ያለው ስራ ለመስራት ስልጠናውን በትኩረት እንድትከታተሉ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

photo 2026 01 26 14 59 37

ስልጠናው በካርታ ዝግጅት ባተኮሩ ርዕሶች ላይ የጽንሰ ሀሳብና የተግባር ስልጠና ከጥር 18 እስከ የካቲት 1/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ከወጣው መርሀ ግብር ለመረዳት ተችሏል።

photo 2026 01 26 14 59 38