የተቋሙ ሪከርድና ማህደር የስራ ክፍል በአዲስ መልክ ታድሶ አገልግሎት መስጠት ጀመረ

photo 2025 10 21 17 37 28

ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋናው መስሪያ ቤት የሪከርድና ማህደር የስራ ክፍል በአዲስ መልክ ታድሶ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

photo 2025 10 21 17 37 30 2


የሪከርድና ማህደር ክፍል ሰራተኞችለስራ ፍፁም ምቹ ያልነበረውን የስራ ክፍል ለሀገሪቱ ተመሳሳይ ተቋማት ሞዴል መሆን በሚችል ደረጃ ለሠራተኞችና በክፍሉ ለሚሰጠው አገልግሎት ምቹ ሆኖ እንዲታደስ ለሰሩት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

photo 2025 10 21 17 37 29


የስራ ክፍሉ ለአገልግሎት ክፍት ያደረጉት ዋና ዳይሬክተሩ ባለፉት ሶስት ዓመታት በተቋሙ ሁለንተናዊ ለውጥ ለማምጣት የተሰሩ የሪፎርም ስራዎች በተቋሙ የተልዕኮ አፈፃፀም ላይ የራሳቸውን አዎንታዊ ተፅዕኖ እየፈጠሩ እንደሆነ አንስተው በሪከርድና ማህደር የስራ ክፍል የተሰራው ደረጃውን የጠበቀ የስራ ቦታ በሁሉም የተቋሙ የስራ ክፍሎች ተደራሽ እንዲሆን በጋራ ጠንክረን መስራት አለብን ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

565272588 801475489437675 3211293519904440505 n
567556897 801475566104334 8054081349388223297 n
photo 2025 10 21 17 37 33