የተቋሙ የሪፎርም ሥራዎች ተጎበኙ

548195141 776333711951853 5262197510050920850 n

መስከረም 12/2018 ዓ.ም
በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ባለፉት ሦስት ዓመታት የተሠሩት ሁሉ አቀፍ ተቋማዊ ሪፎርም ሥራዎች በክብርት ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ በተመራው የሥራ ቡድን ተጎበኘ፡፡

550895039 776333161951908 4437091821008354154 n


የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በከር ሻሌ ባለፉት ሦስት ዓመታት በተቋማዊ ሪፎርም የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን የተገኙት ውጤቶች በሚመለከት ገለፃ ያቀረቡ ሲሆን የተቋማቸው አመራርና መላው ሠራተኛ ተቋሙን የዘርፉ ልህቀት ማዕከል ለማድረግ በቅንጅት እያሠሩ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

551143467 776332898618601 4898277729169289355 n


ክብርት ሚኒስትሯ ጋር የነበሩት የሚኒስትር መ/ቤት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተቋሙ የተከናወኑ ተግባራት ለሌሎች ተቋማት እንደ ሞዴል የሚወሰድ መሆኑን ገልፀው ተቋሙ በሀገራችን ለሚከናወኑ የማህበራዊ፣ የኢኮኖሚያዊናየስነ_ህዝብ ዘርፍ ዕቅዶች፣ ፖሊሲና ስትራቴጂ ለማዘጋጀት የሚያስፈልጉት የኦፊሴላዊ መረጃ ምንጭ በመሆኑ ሚኒስትር መ/ቤታቸው የተቋሙ የመረጃ የማመንጨት አቅም የበለጠ ለማሣደግ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደሚደረግ ገልፀዋል፡፡

551984670 776333018618589 708241624778874741 n


ክብርት ሚኒስትሯ በአካል ተገኝተው ከጎበኙና ከቀረበላቸው ገለፃ በተቋሙ ፈጣንና ውጤታማ የሪፎርም ሥራዎች እየሠሩ እንደሆነና በተገኙት ውጤቶችም በጣም ደስተኛ መሆናቸው ገልፀው ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው በቀጣይም በተቋሙ ረጅም እና አጭር ጊዜ ዕቅዶች ላይ በመመስረት የሚያደረገው ድጋፍ በተሻለ ሁኔታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡

550463337 776333335285224 3267889274626615160 n
552004550 776332878618603 5117765739479802135 n
552408767 776333048618586 746345515089947221 n
550852959 776332875285270 2302397397190202128 n