የካቲት 6/2018 ዓ.ም አርባ ምንጭ፣

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ባለፉት ስድስት ወራት ያከናወናቸው ስራ አፈፃፀም የተቋሙ ከፍተኛ አመራር፤ የዋና መስሪያ ቤትና የ26ቱ ቅ/ጽ/ቤት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ ተገመገመ።

ተቋሙ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ያከናወናቸው ተግባራት አፈፃፀም ዝርዝር ሪፖርት በስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ አቶ ሁሴን አጎናፍር ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን የተቋሙ የስድስት ወራት አጠቃላይ አፈፃፀም 90.3 በመቶ መሆኑ በቀረበው ሪፖርት ተገልጿል። በስራ አፈፃፀም የግምገማ መድረኩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ያከናወናቸው ተግባራት አፈፃፀም የተገኙትን ውጤታማ ተሞክሮዎች አጠናክረው በማስቀጠል ቀጣዩን ቀሪ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ተግባራት በተሟላ መልኩ ለማጠናቀቅ በትጋት መረባረብ እንደሚጠባቅባቸው የሥራ መመሪያ ሰጥቷል።


የተቋሙን የስድስት ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ለማድረግ ወደ በአርባ ምንጭ ከተማ ለመጣው የተቋሙ ከፍተኛ አመራር በከተማው ኤርፖርት በጋሞ አባቶች ለተደረገላቸው አቀባበል ምስጋና አቅርበዋል።






