የተቋሙ የአርባ ምንጭ ስታቲስቲክስ ቅ/ጽ/ቤት አዲሱ የቢሮ ህንፃ ተመረቀ

የካቲት 7/2018 ዓ.ም አርባ ምንጭ፣

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በአርባ ምንጭ ከተማ ያስገነባውን የአርባ ምንጭ ስታቲስቲክስ ቅ/ጽ/ቤት አዲሱን የቢሮ ህንፃ በተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ እና ዶ/ር ደምሴ አድማሱ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳደር ተመረቀ።

631596381 892067650378458 5021747368966372200 n
634130031 892067727045117 2697812348700563741 n

ዶ/ር ደምሴ አድማሱ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳደር ተቋሙ የሚያመነጫቸው የስታቲስቲክስ መረጃዎች ለሀገርና ለዞናቸው የልማት ዕድገት ያላቸውን የላቀ ፋይዳ በማስረዳት በቀጣይም ቅ/ጽ/ቤቱ በዞኑ ለሚያከናውናቸው ስራዎች ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱን ላይ መልእክት ያስተላለፉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ተቋሙ በመላው ሀገሪቱ የሚገኙ የተቋሙ ቅ/ጽ/ቤቶች በሂደት የራሳቸውን ለስራ ምቹ የሆኑ የቢሮ ህንፃ እንዲኖራቸው የሚያስችል ተቋማዊ የሪፎርም ስትራቴጂ ቀርፆ በትኩረት ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን አንስተው ዛሬ በአርባ ምንጭ ከተማ የተመረቀው ቅ/ጽ/ቤቱ የቢሮ የመገልገያ ህንፃ የትኩረቱ አንድ ማሳያ መሆኑን በማስረዳት የከተማ አስተዳደሩ መሬት በማቅረብና ግንባታው በአጠረ ጊዜ እንዲጠናቀቅ ለሰጠው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።

632928854 892067583711798 1456805930213185792 n
634991953 892068130378410 1830176166232978146 n

የቅ/ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ስሜ አንበሴ አዲሱ የቢሮ ህንፃ ከዚህ ቀደም የነበረባቸውን የቢሮ ክፍሎች እጥረትና ለስራ ምቹ ያለመሆን ችግርን በመቅረፍ በዕለት ተዕለት ስራቸው ላይ ከፍተኛ መነሳሳት እንደፈጠረላቸው ገልፀው የህንፃ ግንባታው እውን እንዲሆን ድጋፍ ላደረጉት አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል።

631976012 892067860378437 9219435071671413160 n
628564485 892067887045101 4854657221537739008 n
628526135 892068413711715 4529418127161305678 n