የአስተዳደራዊ መረጃ አሰባበብ፣ አያያዝና ትንተና ለማሻሻል የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ

ሰኔ5/2017ዓ.ም ሀዋሳ፣

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የአስተዳደራዊ መረጃ አመዘጋገብ፣ አያያዝና ትንተና ለማሻሻል የሚያስችል ስልጠና ለሲዳማ ብሔራዊ  ክልላዊ መንግስት ፕላንና ልማት ቢሮ ሀላፊዎችና ባለሙያዎች ሰጠ።

aa3a7653 001

በስልጠናውን መክፈቻ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስታቲስቲክስ ልማትና ሜቶዶሎጂ ዘርፍ  ምክትል ዋና ዳይሬክተር  ወ/ሮ ጀሚላ መሀመድ የአስተዳደራዊ መዛግብት መረጃዎች ለስታቲስቲክስ መረጃ ግብዓት መሆናቸውን አንስተው እንደሀገር ያሉትን  የመረጃ ክፍተቶች ለመሙላትና የክልሎችን አካውንት ለማዘጋጀት አስተዳደራዊ መረጃዎች ለኦፊሴላዊ ስታቲስቲክስ ምንጭ ከፍተኛ  ጠቀሜታ  እንዳላቸው ገልፀዋል። ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ አክለውም የስልጠናው ዋና ዓላማ አስተዳደራዊ መረጃዎች ለሀገራዊ እና  ክልላዊ ስታቲስቲክስ ምርት ያላቸውን አጠቃቀም ለማሳደግ የስታቲስቲክስ ሴክተር አመራሩንና ባለሙያውን በእውቀትና በክህሎት  ለማብቃት ነውሲሉ ገልፀዋል።

aa3a7689

በመድረኩ የተገኙት የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የፕላንና ልማት ቢሮ ሀላፊ  ዶ/ር አራርሶ ገረመው መረጃ ለእቅድ ዝግጅት፣ ፖሊሲ ለማውጣት ወሳኝ በመሆኑ ወቅታዊ፣ ተነፃፃሪና ጥራት ያለው የአስተዳደራዊ  መረጃ  አመዘጋገብና አያያዝ አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት የዛሬው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መዘጋጀቱን ገልፀዋል።

aa3a7639 004

ስልጠናው በስታቲስቲክስ ፅንሰ ሀሳብ፣ የመረጃ አመዘጋገብ ዘዴዎች፣ አያያዝና ትንተና ፣ የመረጃ ጥራት፣ የመረጃ ቅብብሎሽ፣ የቴክኖሎጂ  አጠቃቀም፣የመረጃ ቋት አደረጃጀት፣ መረጃ ለመተንተን የሚረዱ ሶፍትዌሮችና የስታቲስቲክስ ህግ ያተኮሩ ርዕሶች ላይ በኢትዮጵያ  ስታቲስቲክስ አገልግሎት የአስተዳደር መረጃ ቅንጅት ፣ስታንደርድና ጥራት መሪ ስራ አስፈፃሚ ከፍተኛ ባለሙያዎች ከሲዳማ ብሔራዊ ክልል፣ ከአራቱ የሲዳማ ዞኖች፣ ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ለተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች እየተሰጠ ይገኛል።

aa3a7710
aa3a7736
aa3a7752