የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የቅድመ ዝግጅት ስራ ተጀመረ

ሐምሌ 8/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣

1t8a0620.jpg

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2018ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ለሚካሄደው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የቅድመ ዝግጅት ስራ መጀመሩን በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት በተጋጀው የማስጀመሪያ ፕሮግራም ይፋ አደረገ።

1t8a0636.jpg


በቅድመ ዝግጅት ተግባራት የቆጠራው ስነ ዘዴ፣ የሰው ሀይል ዝግጅት፣ ለመስክ ስራ የሚውሉ ግብዓቶችና የቴክኖሎጂ ዝግጅት በዋናነት እንደሚከናወኑ የተገለፀ ሲሆን ይህን ስራ የሚያስተባብር ኮሚቴ ከዛሬ ጀምሮ እነዚህን ስራዎች ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በታቀደው ጊዜ ለማጠናቀቅ ወደ ስራ መግባቱን የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ገልፀዋል።

1t8a0610.jpg


ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም ይህ ስራ ከመስከረም ወር ጀምሮ በመላ ሀገራችን ባሉ ከትናንሽ እስከ ትላልቅ የምርትና የንግድ ድርጅቶች ቆጠራ እንደሚካሄድ በመረዳት በየደረጃው ያለው የመንግስት አደረጃጀት፣ በዚህ ቆጠራ መረጃ ሰጪ የሆኑ የኢኮኖሚ ድርጅት ባለቤቶችና መላው የሀገራችን ህብረተሰብ ለስራው ስኬት አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

1t8a0638.jpg