የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የመጀመሪያ ዙር አፈፃፀምና የሁለተኛ ዙር ቆጠራ ዝግጅት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደረገ

1t8a7401

ታህሳስ 14/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከጥቅምት 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ እያካሄደ በሚገኘው የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የመጀመሪያ ዙር የቆጠራ አፈፃፀምና የሁለተኛ ዙር ስራ ዝግጅት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ውይይት አደረገ።

1t8a7406

በውይይት መድረኩ ላይ የቆጠራው የመጀመሪያ ዙር የስራ አፈፃፀም በቢዝነስ ስታቲስቲክስ ስራ አስፈፃሚ አቶ ናቃቸው ነጋሽ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ባለድርሻ አካላትም በቀረበው ሪፖርት መሰረት የቆጠራው አፈፃፀምላይ ሀሳብ፣ አስተያየትና ለቀጣይ ስራ ግብዓት የሚሆን ሀሳቦችን አንስተዋል።

1t8a7409

በመጨረሻም የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ከተሳታፊዎች ለተነሱ አስተያየትና ጥያቄዎች ሰፊ የሆነ ማብራሪያና ምላሽ የሰጡ ሲሆን ከመጀመሪያ ዙር የተገኘውን ግብዓት በመውሰድ ሁለተኛ ዙር ቆጠራው በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ ገልፀዋል።

1t8a7411
1t8a7410