
አዲስ አበባ፣ ኅዳር 24/2018 ዓ.ም፣
የገንዘብ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት ሠራተኞች ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀን “ትውልድን በሥነ ምግባር፤ ተቋምን በአሠራር” በሚል መሪ ቃል በጋራ አከበሩ።

የሁለቱ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የተከብረው በዓሉ፣ ሙስና በሃገራችን አሁንም የልማት ፀር መሆኑ ታውቆ ሁሉም በየሥራ ቦታው ከሙስና የፀዳ ስራን በመስራት እና አገልግሎት በመስጠት የተጣለበትን ኃላፊነት መወጣት እንዳለበት መልዕክት ተላልፏል። የተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች ያላቸውን ንብራት ማሳወቂያ ቅጽ ሞልተው ርክክብ ያደረጉ ሲሆን፣ ሙስና በልማት እና በፍትሐዊነት ላይ እያደረሰ ያለውን ተጽዕኖ በሚመለከት የተዘጋጀ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይት እና የግንዛቤ መፍጠር ስራ ተሰርተዋል።




