የፍትሐ ብሔር ሥነ-ሥርዓትና በወንጀል ጉዳዮች ህግ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

1t8a8089

ታህሳስ 24/2018 ዓ.ም አዳማ፣

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የፍትሐ ብሔር ሥነ_ሥርዓትና በወንጀል ጉዳዮች ህግ ላይ ከ26ቱ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለተውጣጡ የሰው ሀብት ባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

1t8a8078

በመድረኩ ተገኝተው የስልጠናውን መክፈቻ ያደረጉት የተቋሙ የዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ኃላፊ ተቋሙ በሚያከናውናቸው የሰው ሀይል ቅጥር፣ ከዋስትና ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣ በንብረት አያያዝ ላይ ለሚያጋጥሙ የህግ ጉዳዮች የሚያግዝ ስልጠና መሆኑን ገልፀው ፣ በዚህ ስልጠና የምትሳተፉ ባለሙያዎች የተቋሙ ሀብትና ንብረት ጠባቂ በመሆናችሁ ስልጠናውን በትኩረት በመከታተል በስራ ላይ እንድታውሉ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

1t8a8091

ስልጠናው በፍትሐ ብሔር ስነ ስርዓት ህግ፣ ዓላማ፣ በወንጀል ጉዳዮች፣ በክስ አመሰራረት፣ የክስ ማመልከቻ አዘገጃጀትና ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከፍትሕ ሚኒስቴር በመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች እየተሰጠ ይገኛል።

1t8a8085

የስልጠናው ተሳታፊዎች የተነሱት ርዕሶች ላይ ከስራ ጋር ከሚያጋጥሟቸው ከሰው ኃይል፣ ከዋስትና ጋር ለተያያዙ ጉዳዮች ጠቃሚ መሆናቸውንና ለስራቸው ጠቃሚ ግንዛቤ እንዳገኙበት ገልፀዋል።

1t8a8093