የ2018 የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የቅድመ አሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

ሐምሌ 9/2017ዓ.ም አዳማ ፣

1t8a0689


የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አግልግሎት በ2018ዓ.ም ለሚያካሄደው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የቅድመ አሰልጣኞች ስልጠና ከዋና መሠሪያ ቤትና 26ቱ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለተወጣጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች እየተሰጠ ይገኛል።

1t8a0684


የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2018ዓ.ም የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ለማካሄድ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እያከናወነ መሆኑን አንስተው ከነዚህ የቅድመ ዝግጅት ተግባር መካከል አንዱ በየደረጃው በቆጠራው ስራ የሚሳተፈውን የሰው ሀይል በጥራት አሰልጥኖ ለስራው ዝግጁ ማድረግ ሲሆን ዛሬ በሚጀመረው ስልጠና የሚሳተፉ ሰልጣኞች በቀጣይ በቆጠራው መስክ ስራ የሚሳተፈውን የሰው ሀይል የመሰልጠን ትልቅ ሀላፍነት ያለበቸው መሆኑን በመገንዘብ ስልጠናውን በከፍተኛ ትኩረትና ስነ-ምግባር መከታተል እንደሚጠበቅባቸው መመሪያ በመስጠት ስልጠናውን አስጀምረዋል።

1t8a0652
1t8a0657


ስልጠናው ከሐምሌ 9 ጀምሮ ለቀጣይ 20 ቀናት በቆጠራው ስነ ዘዴ፣ ፅንሰ ሀሳብ፣ የቆጠራው መጠይቆች፣ መረጃውን ለመሰብሰብ የሚውሉ ሶፍትዌርና የታብሌት ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ የተሟላ ዕውቀትና ግንዛቤ ለመፍጠር በሚያስችል ደረጃ በተቋሙ የቢዝነስ ስታቲስቲክስ ከፍተኛ ባለሙያዎች እንደሚሰጥ ከስልጠናው መርሀ ግብር ለማወቅ ተችሏል። በስልጠናው ከዋናው መስሪያ ቤትና ከቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የተውጣጡ በቁጥር 236 የሚሆኑ ባለሙያዎች ይሳተፉበታል።

1t8a0676
1t8a0662