በግብርና ቆጠራ አፈፃፀም ከአለም አቀፍ የምግብና ግብርና ድርጅት (FAO) ጋር ውይይት ተደረገ

ግንቦት 19/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2017ዓ.ም እያካሄደ በሚገኘው የግብርና ቆጠራ አፈፃፀምና በቀጣይ ቀሪ የቆጠራው ተግባራት ላይ  ከአለም አቀፍ የምግብና ግብርና ድርጅት (FAO) ጋር ውይይት አደረገ።

የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ተቋሙ ለሁለተኛ ጊዜ እያካሄደ የሚገኘውን የግብርና ቆጠራ ከፍተኛ በሆነ በመንግስትና አጋር ድርጅቶች ድጋፍ አሁን  ያለበት ውጤታማ የሆነ አፈፃፀም ላይ መድረሱን ገልፀው አለም አቀፍ የምግብና ግብርና ድርጅት (FAO) እያደረገ ላለው የቴክኒክ ድጋፍ በተቋሙ ስም አመስግነዋል። ተቋሙ በቀጣይ ቀሪ የቆጠራው ተግባራት ከድርጅቱ የቴክኖሎጂና  የቴክኒክ  ድጋፍ እንደሚፈልግም ዋና ዳይሬክተሩ አክለው ገልፀዋል። 

aa3a9676

የአለም አቀፍ የምግብና ግብርና ድርጅት (FAO) የግብርና ቆጠራ ቡድን መሪ ሄሮ ካስታኖ (Ph.D) የግብርና ቆጠራው ጥሩ አፈፃፀም ላይ እንደሆነ እና በቀጣይ ቀሪ ስራዎች ላይ ከተቋሙ ጋር በጋራ እንደሚሰሩ ገልፀዋል። 

photo 2025 07 18 11 51 42

የግብርና ቆጠራ ከቅድመ ዝግጅት አሁን እስካለበት ደረጃ ያለውን አፈፃፀም እንዲሁም ቀሪ ተግባራትን የሚያሳይ ገለፃ በግብርና  ስታቲስቲክስ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ አብዱላዚዝ ሽፋ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች  በኢኮኖሚ ስታቲስቲክስ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ቀሬና በተቋሙ ከፍተኛ ባለሙያዎች ምላሽ ተሰቶበታል።