የፍልሰት መረጃ ለማጋራት የተፈረመው መግባቢያ ሰነድ ትግበራ ላይ ውይይት ተደረገ

1t8a7550

ነሐሴ 20/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣

የፍልሰት መረጃ ለማጋራት ከዚህ ቀደም በብሔራዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት መካከል የተፈረመው መግባቢያ ሰነድ ትግበራ ላይ ለመወያየት የተዘጋጀ ወርክሾፕ በአዲስ አበባ ተጀመረ።

1t8a7528

የኢትዮጵያ መንግስት ፍልሰትን ለማስተዳደር ብሔራዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት አቋቁማ በመስራት ላይ እንደምትገኝ የገለፁት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ  የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ሀገራዊ የፍልሰት የመረጃ ፍላጎትን ለማሟላት ተቋሙ በሚያከናውናቸው ናሙና ጥናቶች ውስጥ የፍልሰት መጠይቅን በማካተት ከተለያዩ ጥናቶች ጋር በማቀናጀትና ከአስተዳደራዊ መዛግብት የፍልሰት ስታቲስቲክስን ለማመንጨት እየተሰራ እንደሚገኝ በመስረዳት በዚህ ወርክ ሾፕ መግባቢያ ሰነዱን ወደ ተግባር ለማስገባት የሚያስችል አስቻይ ሁኔታዎችን መተንተን፣ ክፍተቶችን በመለየትና የመፍትሔዎችን በማመላከት የአጭር እና የረጅም የትግበራ እቅድ ማዘጋጀት ከትብብር ጥምረቱ ቡድን እንደሚጠበቅ መልዕክት አስተላልፈው፤ይህ ወርክ ሾፕ እንዲዘጋጅና እውን እንዲሆን ድጋፍ ያደረገልን እንዲሁም ሁሌም የቀጠናውን የስታቲስቲክስ መረጃ ለማሻሻል አባል ሀገራትን ለመደገፍ ያለሰለሰ ጥረት ለሚያደርገው IGAD ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

1t8a7480

በዚህ ውይይት ላይ በመሳተፍ ላይ የሚገኙ የዓለም አቀፍ ተቋማት IOM Ethiopia, UNHCR, ILO, UN-WOMEN የፍልሰት መረጃ አስተዳደርን ለመደገፍ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልፀዋል።

1t8a7468
1t8a7495
1t8a7576
1t8a7581