በተቋማቱ መካካል የልምድ ልውውጥ መርሀ-ግብር እየተደረገ ይገኛል

1t8a9948

መስከረም 26/2018ዓ.ም አዲስ አበባ፣

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2017ዓ.ም ባካሄደው የግብርና ቆጠራ የተገኙትን ልምዶች ለናሚቢያ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ የማካፈል የስልጠና መርሀ-ግብር በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት እየሰጠ ይገኛል።

1t8a9883

በመድረኩ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የግብርና ዘርፍ ስታቲስቲክስ መረጃዎች ከአመታዊ የግብርና ናሙና ጥናት በመሰብሰብ፣ በማጠናቀርና ሪፖርት አዘጋጅቶ ለመንግስትና ለሌሎች የዘርፋ መረጃ ተጠቃሚዎች ተደራሽ በማድረግ የብዙ አመታት ልምድ ያካበተና በአፍሪካ አህጉርም ቀዳሚ ተቋም መሆኑን አንስተው ተቋማቸው ከዚህ ቀደም ለዘመናት በስራ ውስጥ ያካበተውንና በ2017ዓ.ም ለሁለተኛ ጊዜ ባካሄዳው የግብርና ቆጠራ የተገኙትን ልምዶችና ተሞክሮዎች ለናሚቢያ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ለማካፈል ዕድሉ በማግኘታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው የዚህ አይነቱ በአፍሪካ ሀገራት አቻ ተቋማት መካካል የሚደረገው የልምድ ልውውጥ በአህጉረ አፍሪካ ጠንካራ የስታቲስቲክስ ተቋማት ግንባታ ስትራቴጅ አካል በመሆኑ በቀጣይም ተጠነክሮ መቀጠል እንደሚገባው መልዕክታቸውን በማስተላለፍ መርሀ-ግብሩን አስጀምረዋል።

1t8a9927

የስታቲስቲክስ ዲጂታላይዜሽን ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሜሮን ክፈለው እንዳሉት የመድረኩ ዓላማ ተቋማችን በስታቲስቲክስ ልማት ፕሮግራም (ከ2016 -2018ዓ.ም)በመካከለኛ ዘመን እቅድ ካከናወናቸው ተግባራት  አንዱ በ2017 ዓ.ም የተካሄደው የግብርና ቆጠራ ከመስክ መረጃ የመሰብሰብ ተግባር አጠናቀን መረጃ የማጥራት የሪፖርት ዝግጅት ስራ ላይ እንገኛለን ያሉ ሲሆን ከግብርና ቆጠራ ያገኘናቸውን ስኬቶችና ያጋጠሙን ችግሮች የተወጣንበትን መንገድ ልምድ ለማካፈል ሲሆን ናሚቢያ ስታቲስቲክስም ያሉትን ልምዶች ለመጋራት ዝግጁ ነን ሲሉ ገልፀዋል።

1t8a9931

በመድረኩ የናሚቢያ የኢኮኖሚ ስታቲስቲክስ ዘርፍ ኃላፊና የልኡክ ቡድኑ መሪ ዶ/ር ማቡኩ ሙቡሲሲ ስለናሚቢያ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ አጠቃላይ ገለፃ ቀርቦ  አቅርቦው ስለተቋማቸው ግንዛቤ አስጨብጠዋል።

1t8a9931

የልምድ ልውውጥ መርሀ ግብሩ ለሚቀጥሉት አምስት ቀናት እንደሚቀጥል ከወጣው መርሀ ግብር ለመረዳት ተችሏል።

1t8a9969
1t8a9827