አስተዳደራዊ መረጃዎች ለኦፊሺያል ስታቲስቲክስ መረጃ ምንጭነት መጠቀም በሚያስችል ስነ-ዘዴ ላይ ስልጠና ተሰጠ

1t8a4613

ህዳር 10/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከስታቲስቲክስ ኖርዌይ ጋር በመተባበር የአስተዳደራዊ መረጃዎችን ለኦፊሺያል ስታቲስቲክስ መጠቀም የሚያስችል ስልጠና ከፌዴራል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ለተውጣጡ ባለሙያዎች ተሰጠ።

1t8a4644


በስልጠናው መድረክ ተገኝቷ መልዕክት ያስተላለፋ የስታቲስቲክስ ኖርዌይ አቅም ግንባታ ፕሮጀክት አማካሪ ሚስተር ሳዲቅ ኪዌሲ ስታቲስቲክስ ኖርዌይ ከኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ጋር በተለያዩ የስታቲስቲክስ አቅም ግንባታ ተግባራት ላይ በትብብር እየሰራ መሆኑን አንስተው የዛሬው ስልጠናም አስተዳደራዊ መረጃዎች ለኦፊሺያል ስታቲስቲክስ መረጃ ምንጭነት መጠቀም በሚያስችል ስነዘዴ ላይ በአስተዳደራዊ መረጃ ላይ ለሚሰሩ የሴክተር መስሪያ ቤት ባለሙያዎች ግንዛቤ ለመፍጠር የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል። በስልጠናው አስተዳደራዊ መረጃዎች አጠቃቀም፣አደረጃጀት፣ከአስተዳደራዊ መረጃዎች ጥራት ያለው ኦፊሺያል ስታቲስቲክስ መረጃዎች ማመንጨት በሚያስችል ስነዘዴ ላይና ሌሎች ርዕሶች ላይ በዘርፋ የካበተ ልምድና ዕውቀት ባለቸው የስታቲስቲክስ ኖርዌይና የተቋሙ ባለሙያዎች ገለፃ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

1t8a4620


በስልጠናው ከገቢዎች ሚኒስቴር፣ ከንግድ ሚኒስቴር፣ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ ከሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲና ሌሎች ተቋማት የተውጣጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

1t8a4622