የመንግስት ሰራተኞች የቁጥር መረጃ የማረጋገጥ ስራ ለማከናዋን የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እየተከናወነ ይገኛል

ህዳር 15/2018ዓ.ም አዳማ፣

1t8a4726

የሲቪል ሰርቪስ ከኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ጋር በመተባበር በመላ ሀገሪቱ የሚገኙትን የመንግስት ሰራተኞች ቁጥር መረጃ የማረጋገጥ የሙከራ ተግባራት ላይ ለሚሰተፉ መረጃ ሰብሳቢዎች ስልጠና በአዳማ መስጠት ተጀመረ።

1t8a4747

በስልጠናው ማስጀመሪያ መድረክ ላይ የተገኙት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ ሽብሩ አባዲማ ተቋማቸው ቀልጣፋና ውጤታማ ህዝብ አገልጋይ የሲቪል ሰርቪስ ለመፍጠር ሪፎርም በማካሄድ በአሁኑ ጊዜ ወደ ተሟላ ትግበራ ለመግባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ገልፀው የሪፎርሙን ቀጣይነት ለማረጋገጥ በመንግስት ተቋማት ተቀጥረው የሚሰሩ ሰራተኞች ቁጥር ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ የተረጋገጠ መረጃ መያዝ አስፈላጊ በመሆኑ በሀገራችን የሚገኙትን ሰራተኞች መረጃ ለመረጋገጥ በዘርፉ የካበተ ልምድና እውቀት ካለው የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ጋር ለመስራት የሚያስችል ቅድመ ሁኔታ ተጠናቆ ዛሬ ለስራው የሚያስፈልገውን የቅድመ ዝግጅት ተግባር በመስክ መረጃ ሰብሳቢዎች ስልጠና ማስጀመራቸውን ገልፀዋል።

1t8a4718

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ በሀገራችን በመንግስት መስሪያ ቤት ተቀጥረው የሚሰሩትን  ሰራተኞች ቁጥር መረጃ የማረጋገጥ ስራ ከተቋማቸው ጋር ለመስራት በመወሰኑ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው፤ ተቋማቸው በዘርፉ ያለውን ልምድ፣ ዕውቀት፣ ቴክኖሎጂና መሰረተ ልማት በማስተባበር ይህን  ለሀገርና ለኮሚሽኑ ከፍተኛ ትርጉም ያለው ተግባር በጊዜና በጥራት ሰርቶ ለማስረከብ በትጋት እንደሚሰራ ገልፀዋል።

1t8a4730

ለስራው ከተለያዩ የሀገርቱ ዩኒቨርሲቲ ለተወጣጡ መምህራኖች ለሚቀጥሉት አምስት ቀናት የሰራተኞች ቁጥር መረጃ ለማረጋገጥ በተዘጋጁ ስነ-ዘዴዎችና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዩች ላይ የጽንሰ ሀሳብና የተግባር ስልጠና እንደሚሰጥ ከስልጠናው መርሀ-ግብር ለመረዳት ተችሏል።

1t8a4727
1t8a4715