በዋጋ ስታቲስቲክስ ጥናት ላይ ስልጠና ተሰጠ

a3a9795

መጋቢት 14/2018 ዓ.ም አዳማ፣

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየወሩ በሚያወጣው የዋጋ ስታቲስቲክስ ጥናት መረጃ ላይ ከ26ቱ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለተውጣጡ የዋጋ ስታቲስቲክስ መረጃ ሰብሳቢዎች፣ ተቆጣጣሪዎችና ስታቲስቲሺያኖች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

a3a9789

የስልጠናውን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2017 ዓ.ም ትላልቅ ቆጠራና ጥናቶችን ማካሄዱን አንስተው የዋጋ ጥናት መረጃ በየወሩ የሚሰራ፣ የማይቋረጥ አስፈላጊና ወሳኝ የማክሮ ኢኮኖሚ ግብዓት በመሆኑ ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው መረጃ መሆኑን ገልፀው፤ በዚህ ጥናት የመስክ ስራ ላይ የተሰማራችሁ መረጃ ሰብሳቢዎች፣ ስታቲስቲሺያኖችና ተቆጣጣሪዎች ስልጠናውን በመከታተል ጥራት ያለው የዋጋ ስታቲስቲክስ መረጃ መሰብሰብ አለባችሁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

a3a9831

የዋጋ ስታቲስቲክስ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ አለማየሁ ተፈሪ ይህ ስልጠና የተዘጋጀበት ዋና ዓላማ በመስክ ስራ ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየትና በመፍታት ለመረጃ ጥራት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለው ገልፀው፤ በዋጋ ስታቲስቲክስ ጥናት ፅንሰ ሃሳብ፣ ስለጥናቱ አስፈላጊነትና የመረጃ ጥራት ላይ ያተኮረ ገለፃ ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሯል።

a3a9837

ስልጠናው ከ26ቱ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለተውጣጡ በመስክ ስራ ላይ ለሚሳተፉ 300 የሚሆኑ ባለሙያዎች ለቀጣይ ሰባት ቀናት እንደሚሰጥ ከወጣው መርሀ ግብር ለመረዳት ተችሏል።

a3a9853
a3a9842 1
a3a9862