የ ኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት
የእርስዎ አስተማማኝ የመረጃ ምንጭ ከ1956 ዓ.ም

የሕዝብ ትንበያ 2017 ዓ.ም
0
ብሄራዊ የስራ አጥነት መጠን(2013)
0 %
የሰኔ ወር 2017 ዓ.ም የሸማቾች ዋጋ መረጃ ጠቋሚ
0 %
ዓመታዊ ምርት በኩንታል(2013-2014)
0
ESS Publications Report

የስታቲስቲክስ መዝገብ ቋት

በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ለመስጠት አስተማማኝ ስታቲስቲካዊ ሪፖርቶችን እና ህትመቶችን ይመልከቱ።

Ethiopia Data Bank

ስታትባንክ

የእርስዎ አጠቃላይ እና ወቅታዊ ስታቲስቲካዊ መረጃ ምንጭ።

calendar svgrepo com 1

የስታቲስቲክ ካሌንደር

አስፈላጊ ስታቲስቲካዊ መረጃዎችን እና ኩነቶችን ለማቀድ እና የመከታተያ ግብዓት።

ሰኔ 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስርዓተ ፆታና የአካል ጉዳተኞች ስታቲስቲክስ መረጃዎችን በጥናት፣ በቆጠራና በአስተዳደራዊ መዛግብት መረጃዎች ለማካተት የሚያስችል መመሪያ ላይ ከተቋሙ መሪ ስራ አስፈፃሚዎች ጋር ውይይት አደረገ። በውይይት መድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የስነ-ሕዝብና ማህበራዊ ስታቲስቲክስ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ አይናለም ተሻገር የስርዓተ ፆታና የአካል ጉዳተኞች ስታቲስቲክስ የመረጃ ክፍተት መኖሩን ገልፀው ፤ ተቋሙ በሚያዘጋጃቸው የጥናትና ቆጠራ መረጃዎች ወጥና አለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የስርዓተ ፆታና የአካል ጉዳተኞች ስታቲስቲክስ መረጃዎች እንዲካተቱ ለማስቻል መመሪያው መዘጋጀቱን አንስተው ሁሉም ጥናትና ቆጠራ የሚያከናውኑ የስራ ክፍሎች ለመመሪያው ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦች እንዲሰጡ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል። የስርዓተ ፆታ፣ የአካል ጉዳተኝነት ስታቲስቲክስ መረጃዎችን ከጥናትና ቆጠራ

ሰኔ 05/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የመንግስት አገልግሎት እና የአስተዳደር ሪፎርምን አስመልክቶ ለዋናው መስሪያ ቤት ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ። ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የተቋሙ የስታቲስቲክስ ዲጂታላይዜሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር

ሰኔ5/2017ዓ.ም ሀዋሳ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የአስተዳደራዊ መረጃ አመዘጋገብ፣ አያያዝና ትንተና ለማሻሻል የሚያስችል ስልጠና ለሲዳማ ብሔራዊ  ክልላዊ መንግስት ፕላንና ልማት ቢሮ ሀላፊዎችና ባለሙያዎች ሰጠ። በስልጠናውን መክፈቻ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስታቲስቲክስ ልማትና ሜቶዶሎጂ ዘርፍ  ምክትል ዋና ዳይሬክተር  ወ/ሮ ጀሚላ መሀመድ የአስተዳደራዊ መዛግብት መረጃዎች ለስታቲስቲክስ መረጃ ግብዓት መሆናቸውን አንስተው እንደሀገር ያሉትን  የመረጃ ክፍተቶች ለመሙላትና የክልሎችን አካውንት ለማዘጋጀት አስተዳደራዊ መረጃዎች ለኦፊሴላዊ ስታቲስቲክስ ምንጭ ከፍተኛ  ጠቀሜታ  እንዳላቸው ገልፀዋል። ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ አክለውም የስልጠናው ዋና ዓላማ አስተዳደራዊ መረጃዎች ለሀገራዊ እና  ክልላዊ ስታቲስቲክስ ምርት ያላቸውን አጠቃቀም ለማሳደግ የስታቲስቲክስ ሴክተር አመራሩንና ባለሙያውን በእውቀትና በክህሎት  ለማብቃት ነውሲሉ ገልፀዋል። በመድረኩ የተገኙት የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የፕላንና ልማት ቢሮ ሀላፊ  ዶ/ር አራርሶ ገረመው መረጃ ለእቅድ ዝግጅት፣ ፖሊሲ ለማውጣት ወሳኝ በመሆኑ ወቅታዊ፣ ተነፃፃሪና ጥራት ያለው የአስተዳደራዊ  መረጃ  አመዘጋገብና አያያዝ አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት የዛሬው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መዘጋጀቱን ገልፀዋል። ስልጠናው በስታቲስቲክስ ፅንሰ ሀሳብ፣ የመረጃ አመዘጋገብ ዘዴዎች፣ አያያዝና ትንተና ፣ የመረጃ ጥራት፣ የመረጃ ቅብብሎሽ፣ የቴክኖሎጂ  አጠቃቀም፣የመረጃ ቋት አደረጃጀት፣ መረጃ ለመተንተን የሚረዱ ሶፍትዌሮችና የስታቲስቲክስ ህግ ያተኮሩ ርዕሶች ላይ በኢትዮጵያ  ስታቲስቲክስ አገልግሎት የአስተዳደር መረጃ ቅንጅት ፣ስታንደርድና ጥራት መሪ ስራ አስፈፃሚ ከፍተኛ ባለሙያዎች ከሲዳማ ብሔራዊ ክልል፣ ከአራቱ የሲዳማ ዞኖች፣ ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ለተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች እየተሰጠ ይገኛል።

ሰኔ 2/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት እያካሄደ በሚገኘው ሁለተኛ ዙር የግብርና ቆጠራ አፈፃፀም የተቋሙ ከፍተኛ አመራር ከ26ቱ ቅርንጫፍ ጽሀፈት ቤት ስራ አስፈፃሚዎች ጋር በበይነ መረብ (virtual meeting) በዘጠኝ ወራት ውስጥ የተከናወኑ የግብርና