የመንግስት ሰራተኞችን ፐርሶኔል መረጃ ለማረጋገጥ ለሚሰማሩ የስልጠና አስተባባሪዎች ኦረንቴሽንና የስራ ስምሪት ተሰጠ

ሚያዚያ 5/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

a3a0772

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ለሚያካሂደው የመንግስት ሰራተኞችን ፐርሶኔል መረጃ ለማረጋገጥ በመረጃ ሰብሳቢዎችና ተቆጣጣሪዎች ስልጠና ለሚሰማሩ ከዋናው መ/ቤትና ከሲቪል ሰርቪስ ለተውጣጡ የቴክኒክና የሎጂስቲክ አስተባባሪዎች ኦረንቴሽንና የስራ ስምሪት ተሰጠ።

a3a0724
a3a0751

በመድረኩ የተገኙት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ተቋሙ ከዚህ ቀደም ትላልቅ ሀገራዊ ቆጠራዎችና ጥናቶችን በስኬት ማከናወኑን አንስተው ይህን ሀገራዊ ስራም ከዚህ ቀደም የነበሩትን ልምዶች በመጠቀም ወጥና ፈጠራ በታከለበት መንገድ በቅንጅት በመስራት ለማሳካት እንሰራለን ያሉ ሲሆን ለዚህ ስልጠና በአስተባባሪነት የተመደባችሁ ባለሙያዎች ስልጠናው በተሳካ መንገድ እንዲከናወን ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ ሲሉ የስራ መመሪያ ሰጥተዋል።

a3a0731

በኦረንቴሽኑ ላይ በስልጠናው ላይ ከዋናው መ/ቤት ወደየማዕከላቱ የሚሄዱ አስተባባሪዎች ማድረግ ስለሚጠበቅባቸውና ከሰልጣኞችም ስለሚጠበቁ ተግባራት ገለፃ የቀረበ ሲሆን ከባለሙያዎቹ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።

a3a0730
a3a0785
a3a0775
a3a0784
a3a0737