በተቋሙ ለተከናወኑ የህንፃ ሪኢኖቬሽን ስራዎች እውቅና ተሰጠ

መጋቢት 29/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

a3a0601
a3a0612

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከፍተኛ አመራሮች በተቋሙ ዋና መ/ቤት በተከናወኑ የህንፃ ጥገና፣ ግንባታና ሪኢኖቬሽን ስራዎች ለኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን እውቅና የመስጠት መርሃ ግብር አካሄደ።

በመርሀ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ተቋሙ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ የሪፎርም ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን አንስተው በሪፎርም ተግባሩ የትኩረት አቅጣጫ ከሆኑት እቅዶች ምቹ የስራ ከባቢን መፍጠር አንዱና ዋነኛው መሆኑን ገልፀው፣ ድርጅቱ በተቋሙ ባከናወናቸው የጥገናና የሪኢኖቬሽን ስራ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም ስራው በኃላፊነትና በጥራት የተገነባና ከትውልድ ትውልድ ሊተላለፍ የሚችል መሆኑን ገልፀው በስራው ለተሳተፉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

a3a0617

በመጨረሻም በተቋሙ የተሰሩትን የሪኢኖቬሽን ስራዎች ጉብኝት ተደርጎ በስራው ለተሳተፉ አካላት የዕውቅናና የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።

a3a0557
a3a0545
a3a0487
a3a0390
a3a0654
a3a0660
a3a0650
a3a0575
a3a0692