”የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነፃነት” በሚል መሪ ቃል ላለፋት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ሀገራዊ ጉባኤ ተጠናቀቀ

ግንቦት 12/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

በፕላንና ልማት ሚኒስቴርና በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ሀገራዊ ጉባኤ መጠናቀቁ ተገለፀ።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ በረከት ፍስሀፅዮንና የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል።

dsc06443

ለሶስት ቀናት የተዘጋጀው ሀገራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ አንፃር የተሰሩ ስራዎችና መረጃዎችን ለውሳኔና ፖሊሲ ለማውጣት ከመጠቀም አንፃር በርካታ እመርታዎች የታየበት መድረክ መሆኑን የገለፁት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ በረከት ፍስሀፅዮን በጉባኤው ከስታቲስቲክስ ሉዓላዊነት ጋር በተያያዙ ጉዳዮች፣ ከቴክኖሎጂ አንፃር የተሰሩና በቀጣይ የሚሰሩ ስራዎች፣ ዜጎች በስታቲስቲክስ ስርዓት ስላላቸው ሚና፣ ሀገራችን በቀጣይ ለምታደርገው የሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት ክለሳ (GDP Rebasing) ከተለያዩ ተቋማት ከተውጣጡ ኃላፊዎች ጋር ውይይት የተደረገበትና ግንዛቤ የተፈጠረበት ጉባኤ መሆኑን ተናግረዋል።

dsc06141

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ተቋማቸው ባለፋት ሶስት ቀናት ያስተዋወቃቸው ዋና ዋና ጉዳዮች በስታቲስቲክስ ልማት ፕሮግራም በመካከለኛ ዘመን እቅድ (ከ2016-2018 ዓ.ም) ያከናወናቸው የስነ-ሕዝብና ጤና ጥናት፣ የተቀናጀ የቤተሰብ ጥናት፣ የግብርና ቆጠራና የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ አፈፃፀም፣ ጥናቶችና ቆጠራዎቹን ለማከናወን የተጠቀማቸው ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችና መሳሪያዎች፣ የመረጃ ጥራትና ተዓማኒነት ላይ ትኩረት ማድረጉን ገልፀዋል።

dsc06101

ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም ይህ ሀገራዊ ጉባኤ ስለስታቲስቲክስ ስራዎች ግንዛቤ የተፈጠረበትና ተቋሙ ለሚያደርገው የልህቀት ጉዞ መመሪያ የተላለፈበት መድረክ መሆኑን ገልፀዋል።

dsc06027

በአጠቃላይ በጉባኤውና በኤግዚቢሽኑ ላይ ከ40 የመንግስትና የግል ተቋማትና የሲቪል ማህበራት የተውጣጡ ኃላፊዎችና ከ30 ሺ በላይ ዜጎች ተሳትፈዋል።

dsc06493