በ2018 በጀት ዓመት እቅድ ዝግጅት ላይ ውይይት ተደረገ

ግንቦት 5/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከፍተኛ አመራሮች በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ዋና ዋና እቅዶችና በጀት ዝግጅት ላይ ውይይት አደረጉ።
የኢትዮጵያ ሥነ-ህዝብና ጤና ጥናት ከመስክ መረጃ የመሰብሰብ ተግባር ተጠናቀቀ

ግንቦት 5/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የ2024 ኢትዮጵያ ሥነ-ህዝብ ጤና ጥናት ከመስክ መረጃ የመሰብሰብ ተግባር ማጠናቀቁን ለሀገር አቀፍ አብይ ኮሚቴና አለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች ገለፀ። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ፍፁም አሰፋ መድረኩ የተዘጋጀው አምስተኛ ዙር የኢትዮጵያ ሥነ-ህዝብ ጤና ጥናት ከመስክ መረጃ የመሰብሰብ ተግባር መጠናቀቁንና ጥናቱ አሁን ላይ የደረሰበትን ደረጃ ለማሳወቅ የተዘጋጀ መሆኑን […]
ሙስናና ብልሹ አሠራርን ለመከላከል የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

ሚያዚያ 30/2017 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከፌደራል ሥነ-ምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር “ሙስናን በመከላከል የዜግነት ግዴታዬን እወጣለሁ’’ በሚል መሪ ቃል ሙስና እና ብልሹ አሠራርን ለመከላከል የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ሰራተኞች እየሰጠ ይገኛል። ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ሙስና ለሀገራችን ልማትና ዕድገት ፈተና ሆነው ከቀጠሉት […]
የዘጠኝ ወራት የግብርና ቆጠራ አፈፃፀም ሪፖርት ተገመገመ

ሚያዚያ 29/2017ዓ.ም አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የሁለተኛ ዙር የግብርና ቆጠራ የዘጠኝ ወራት የመስክ ስራ አፈፃፀም ለተቋሙ የግብርና ቆጠራ አስተባባሪ ኮሚቴ ቀርቦ ውይይት ተደረገ። ለውይይቱ መነሻ የሚሆነውን የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት በግብርና ስታቲስቲክስ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ አብዱላዚዝ ሽፋ ቀርቦ ጥልቅ ውይይት የተደረገበት ሲሆን የእስካሁኑ የስራ አፈፃፀም በታቀደው መሰረት በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገምግሟል። […]
የምግብ ዋስትና ስታቲስቲክስ መረጃዎችን ለመተንተን የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ

ሚያዚያ 22/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የስታቲስቲክስ ኖርዌይ ከምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ (COMESA) ጋር በመተባበር የምግብ ዋስትና ስታቲስቲክስ (Food security Statistics) መረጃ ለመተንተን የሚያስችል ስልጠና ለኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የቤተሰብ በጀትና ሌበር ስታቲስቲክስ ባለሙያዎች ተሰጠ። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በርካታ መረጃዎችን በመተንተን ለተጠቃሚዎች የሚያቀርብ ሲሆን በምግብ ዋስትና ስታቲስቲክስ ላይ የሚወጣ መረጃ አለመኖሩን እንደአንድ ክፍተት በመለየት በተቋሙ ያሉ ባለሙያዎችን […]
የስርዓተ ፆታ ስታቲስቲክስ ረቂቅ መመሪያ ላይ ውይይት ተካሄደ

ሚያዚያ 22/2017 ዓ.ም፣አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስርዓተ ፆታ ስታቲስቲክስ መረጃ አሰባሰብና ጥራቱን ለማሻሻል በተዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ዙሪያ ከአጋር የልማት ድርጅቶች ጋር ውይይት አደረገ። ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የተቋሙ የማህበራዊና አካቶ ስታቲስቲክስ መሪ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ አስናቀች ሀብታሙ ተቋሙ ወቅታዊና ተዓማኒ መረጃዎችን በጥራት ለማቅረብ የሚያስችሉ የሪፎርም ስራዎችን ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ አንስተው ዛሬ ለውይይት የቀረበውን የሀገራችን የስርዓተ […]
የፕላንና ልማት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ውይይት አደረጉ

ሚያዚያ 22/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዩች ላይ ውይይት አደረጉ። የውይይት መድረኩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ፍፁም አሰፋ የመንግስት ሰራተኞች የመንግስት የማድረግ አቅም በመሆናቸው በወቅታዊ ሀገራዊ የማህበራዊ፣ የኢኮኖሚያዊና ፓለቲካዊ አቅጣጫ ላይ በየጊዜው የሚደረጉት ለውጦችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ በቂ ግንዛቤ ኖሯቸው በዕውቀት […]
የአስተዳደራዊ መረጃ አሰባሰብ፣አያያዝ እና ትንተናን ለማሻሻል የሚያስችል ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

ሚያዚያ 21/8/2018ዓ.ም አዳማ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የአስተዳደራዊ መረጃ አሰባሰብ ፣ትንተና እና አያያዝ ለማሻሻልና በቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆን የሚያስችል ስልጠና ከደቡብ ኢትዮጵያ፣ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ከደቡብ ምዕራብና ከሲዳማ ክልል ከተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ለተውጣጡ ባለሙያዎች በአዳማ ከተማ እየሰጠ ይገኛል። ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የተቋሙ የስታቲስቲክስ ሲስተም ልማት እና ሜቶዶሎጂ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ጀሚላ መሃመድ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት […]
የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ

ሚያዚያ 4/2017 ዓ.ም አዳማ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የተሽከርካሪ ስምሪትና የነዳጅ አጠቃቀምን በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ የሚያስችል የኢ-ፍሊት ማኔጅመንት ሲስተም ላይ ከዋናው መስሪያ ቤት ለተውጣጡ ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ። በተቋሙ ሪፎርም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራባቸው ካሉት ተግባራት አንዱ የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ መሆኑን የተቋሙ ስራ አመራር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ኤቢሳ አሰፋ የገለፁ ሲሆን የዛሬው ስልጠናም የተሽከርካሪ […]
ለተቋሙ ባለሙያዎች ስለህጋዊ አሰራር ያላቸውን ግንዛቤ ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና ተሰጠ

መጋቢት 19/2017ዓ.ም አዳማ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የተቋሙ ባለሙያዎች ስለህጋዊ አሰራር ያላቸውን ግንዛቤ ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና ከ26ቱ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለተውጣጡ ባለሙያዎች በአዳማ ከተማ እየተሰጠ ይገኛል። ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የተቋሙ የስታቲስቲክስ ሲስተም ልማት እና ሜቶዶሎጂ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ጀሚላ መሀመድ እንዳሉት ተቋሙ በተያዘው አመት ትላልቅ ጥናቶችና የቆጠራ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልፀው ለነዚህ ስራዎች የተሰማራውን […]