የሁለተኛ ዙር የግብርና ቆጠራ አፈፃፀም ሪፖርት በበይነ መረብ (virtual meeting) ግምገማ ተደረገ

ሰኔ 2/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት እያካሄደ በሚገኘው ሁለተኛ ዙር የግብርና ቆጠራ አፈፃፀም የተቋሙ ከፍተኛ አመራር ከ26ቱ ቅርንጫፍ ጽሀፈት ቤት ስራ አስፈፃሚዎች ጋር በበይነ መረብ (virtual meeting) በዘጠኝ ወራት ውስጥ የተከናወኑ የግብርና ቆጠራ፣ የንግድ እርሻዎችና የበልግ ጥናት ተግባራትን ገምግሟል።
የሁለተኛ ዙር ግብርና ቆጠራ የስምንት ወራት የመስክ ስራ አፈፃፀም ተገመገመ

ግንቦት 26/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የሁለተኛ ዙር የግብርና ቆጠራ የስምንት ወራት መስክ ስራ አፈፃፀም በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ተገመገመ። በመላ ሀገራችን እያተከናወነ የሚገኘው ሁለተኛ ዙር የግብርና ቆጠራ ያለፋት ስምንት ወራት መስክ ስራ አፈፃፀም ሪፖርት የተቋሙ ከፍተኛአመራርና የቆጠራው ቴክኒካል ኮሚቴ አባላት በተሳተፋበት መድረክ ቀርቦ በተደረገው ግምገማ የባለፋት ስምንት ወራት የመስክ ስራ አፈፃፀም በታቀደው መሠረት በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑ የተገመገመ ሲሆን በቀጣይ ወራት የሚከናወኑ ቀሪ የመስክ ተግባራት በተቀመጠላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ የስራ መመሪያ ተሰጥቶ የግምገማ መድረኩ ተጠናቋል።
ለቆጠራ ካርታ ዝግጅት የGIS እና Advance Remote Sensing ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ሲሰጠ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ

ግንቦት 25/2017ዓ.ም አዳማ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ለተቋሙ የካርቶግራፊና ጂ አይ ኤስ ባለሙያዎች በካርታ ማካለል፣ GIS እና Advance Remote Sensing ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ሲሰጠ የቆየው የተግባር ስልጠና ተጠናቀቀ። በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አብዱራዛቅ ዑመር የስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩትና የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ለሀገራችን ልማት ዕቅድና ክትትል ግብዓት የሚሆኑ የስታቲስቲክስና ጂኦ ስፓሻል መረጃዎች የማቅረብ ሀላፊነት የተሰጣቸው ተቋማት በመሆናቸው በሁለቱም ተቋማት ያለውን ዕውቀትና ልምድ በተለየዩ አግባቦች ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመው በጋራ በመስራት ላይ እንዲሚገኙ አንስተው ለ15 ቀናት ሲሰጥ ቆይቶ ዛሬ የተጠናቀቀው ስልጠናም የቆጠራ ካርታ ማካለል ስራን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ የGIS እና Advance Remote Sensing ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ያለውን ዕውቀትና ልምድ በተግባር ለማካፈል የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀው፤ ወደተቋማችሁ ስትመለሱ ያገኛችሁትን ስልጠና ተግባራዊ ለማድረግ በትጋት መስራት ይኖርባችኋል ሲሉ በስልጠናው ለተሳተፋት ባለሙያዎች መልዕክት አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስታቲስቲክስ ዲጂታላይዜሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሜሮን ክፈለው በተቋሙ የቆጠራ ካርታ ማካለል ስራ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ የሚታዩ ክፍተቶችን በመለየት ስራውን በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ የባለሙያዎችን ቴክኖሎጂ የመጠቀም አቅም ለማሻሻል ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀው በቀጣይም በካርታ ዝግጅት፣ GISቴክኖሎጂና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ተቋሙ ከስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት በጋራ እንደሚሰራ ገልፀዋል። የስልጠናው ተሳታፊዎችም ለስራቸው ጠቃሚ የሆነ የጽንሰ ሀሳብና የተግባር እውቀት እንዳገኙ ገልፀዋል።
ለተቋሙ ሴቶች የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ

ግንቦት 25/2017ዓ.ም አዳማ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ሴቶችን ለማብቃት የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና ከተቋሙ ዋና መስሪያ ቤትና ከቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለተውጣጡ ባለሙያዎች ሰጠ። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብነት ሀዋዝ እንደተቋም ሴቶችን ማብቃትና ወደ አመራር ማምጣት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራበት መሆኑን አንስተው የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በሰራው ሪፎርም ሴቶችን ወደ አመራር በማምጣት ሌሎች ባለሙያዎችንም ለማብቃት እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል። ስልጠናውን በስርዓተ ፆታ፣ የማካተት ፅንሰ ሀሳብ አስፈላጊነት፣ ስልቶች፣ ተግዳሮቶችና ልዩ ትኩረት የሚፈልጉ የማህበረሰብ ክፍሎች ፍላጎቶች ላይ ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በመጡት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ጌታቸው ካሴ እየተሰጠ ይገኛል። ስልጠናው ከተለያዩ የስራ ክፍል ለተውጣጡ 45 ባለሙያዎች ለቀጣይ ሶስት ቀናት እንደሚሰጥ ከወጣው መርሀግብር ለመረዳት ተችሏል።
የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና መስሪያ ቤት የስራ ጉብኝት አደረገ

ግንቦት 21/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከ2015−2017ዓ.ም በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት የተከናወኑ ዋና ዋና የሪፎርም ለውጥ ስራዎች በተመለከተ የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ በክቡር አቶ ደሳለኝ ወዳጆ የተመራ ቡድን የስራ ጉብኝት አደረገ። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው ተቋሙ በቋሚ ኮሚቴው ከዚህ በፊት ሲጎበኝ የሰጣቸውን አስተያየቶች እንደግብዓት በመውሰድ የሰራቸውን የለውጥ ስራዎች ለማሳየት የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል። ተቋሙ ከ2015−2017ዓ.ም በሪፎርም ያከናወናቸው ዋና ዋና ለውጦች የተቋሙ መዋቅራዊ አደረጃጀት፣ የሰው ሀይል አቅም ግንባታ፣ ምቹ የስራ ከባቢ መፍጠር፣ የጥናት ስነ−ዘዴዎችን ማሻሻልና ሌሎች ሰፊ የመረጃ ልማት ስራዎች የደረሱበት ደረጃ በተመለከተ በስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ አቶ ሁሴን አጎናፍር ሪፖርት ቀርቧል። የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጆ እና አባላት ተቋሙን ከዚህ ቀደም ሲጎበኙ በጣም ብዙ ክፍተቶች የነበረበት መሆኑን አንስተው ዛሬ በመስክ ምልከታው ወቅት የታዩትን መሻሻሎች በማድነቅ ይህ በጎ ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና ለመረጃ ጥራት ከፍተኛ ድርሻ ያላቸውን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶችንም በዚሁ መልኩ የተሻሉ እንዲሆኑ ለማድረግ ትኩረት እንዲሰጥ አስገንዝቧል::
የስርዓተ ፆታና የአካል ጉዳተኞች ስታቲስቲክስ መመሪያ ዝግጅት ላይ ውይይት ተደረገ

ሰኔ 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስርዓተ ፆታና የአካል ጉዳተኞች ስታቲስቲክስ መረጃዎችን በጥናት፣ በቆጠራና በአስተዳደራዊ መዛግብት መረጃዎች ለማካተት የሚያስችል መመሪያ ላይ ከተቋሙ መሪ ስራ አስፈፃሚዎች ጋር ውይይት አደረገ። በውይይት መድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የስነ-ሕዝብና ማህበራዊ ስታቲስቲክስ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ አይናለም ተሻገር የስርዓተ ፆታና የአካል ጉዳተኞች ስታቲስቲክስ የመረጃ ክፍተት መኖሩን ገልፀው፤ ተቋሙ […]
የግብርና ቆጠራ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

ግንቦት 21/2017ዓ.ም አዳማ፣ የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት የግብርና ቆጠራ አስመልክቶ የተቋሙ አመራሮች፣ ባለሞያዎች እና የአለም አቀፉ የምግብና እርሻ ድርጅት (FAO) ተወካዮች በአዳማና ቢሾፍቱ ዙሪያ የመስክ ጉብኝት አካሄዱ። በመስክ ጉብኝቱ የንግድ እርሻዎች ፣ አነስተኛ ይዞታ ያላቸው የቤተሰብ እርሻ እና የእንስሳት እርባታዎች ላይ ምልከታ የተደረገ ሲሆን የግብርና ቆጠራ ስራው በጥሩ ሂደት ላይ እንደሚገኝ ከመስክ ምልከታው ለመረዳት ተችሏል።
በግብርና ቆጠራ አፈፃፀም ከአለም አቀፍ የምግብና ግብርና ድርጅት (FAO) ጋር ውይይት ተደረገ

ግንቦት 19/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2017ዓ.ም እያካሄደ በሚገኘው የግብርና ቆጠራ አፈፃፀምና በቀጣይ ቀሪ የቆጠራው ተግባራት ላይ ከአለም አቀፍ የምግብና ግብርና ድርጅት (FAO) ጋር ውይይት አደረገ። የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ተቋሙ ለሁለተኛ ጊዜ እያካሄደ የሚገኘውን የግብርና ቆጠራ ከፍተኛ በሆነ በመንግስትና አጋር ድርጅቶች ድጋፍ አሁን ያለበት ውጤታማ የሆነ አፈፃፀም ላይ መድረሱን ገልፀው አለም አቀፍ የምግብና ግብርና ድርጅት (FAO) እያደረገ ላለው የቴክኒክ ድጋፍ በተቋሙ ስም አመስግነዋል። ተቋሙ በቀጣይ ቀሪ የቆጠራው ተግባራት ከድርጅቱ የቴክኖሎጂና የቴክኒክ ድጋፍ እንደሚፈልግም ዋና ዳይሬክተሩ አክለው ገልፀዋል። የአለም አቀፍ የምግብና ግብርና ድርጅት (FAO) የግብርና ቆጠራ ቡድን መሪ ሄሮ ካስታኖ (Ph.D) የግብርና ቆጠራው ጥሩ አፈፃፀም ላይ እንደሆነ እና በቀጣይ ቀሪ ስራዎች ላይ ከተቋሙ ጋር በጋራ እንደሚሰሩ ገልፀዋል። የግብርና ቆጠራ ከቅድመ ዝግጅት አሁን እስካለበት ደረጃ ያለውን አፈፃፀም እንዲሁም ቀሪ ተግባራትን የሚያሳይ ገለፃ በግብርና ስታቲስቲክስ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ አብዱላዚዝ ሽፋ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በኢኮኖሚ ስታቲስቲክስ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ቀሬና በተቋሙ ከፍተኛ ባለሙያዎች ምላሽ ተሰቶበታል።
ተቋማቱ በቀጣይ በትብብር ለመስራት የሚያስችል ውይይት አደረጉ

ግንቦት 11/2017ዓ.ም፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎትና ኖርዌይ ስታቲስቲክስ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በበይነ መረብ (Virtual meeting) ውይይት አደረጉ። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2024/25ከኖርዌይ ስታቲስቲክስ ጋር በነበሩት ፕሮጀክቶች በርካታ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች የልምድ ልውውጦች መገኘታቸው ተገልጿል። በቀጣይ በሚኖረው ፕሮጀክትም በቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ፣ በጥናት ስነ-ዘዴ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ትኩረት የሚሰጣቸው ተግባራት መሆናቸው በውይይቱ ተነስቷል።
በአስተዳደር ዘርፍ የዘጠኝ ወራት ስራ አፈፃፀም ግምገማ ተደረገ

ግንቦት 11/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የተቋሙ ከፍተኛ አመራር በ2017በጀት ዓመት በአስተዳደር ዘርፍ በዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ተግባራት ላይ ከሚመለከታቸው ስራ አስፈፃሚዎች ጋር የስራ ግምገማ አደረገ። በግምገማ መድረኩ በ2017በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት በአስተዳደር ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት በስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ አቶ ሁሴን አጎናፍር ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። በመጨረሻም የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት ውስጥ የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገቡን ገልፀው በቀሩት ቀጣይ ጊዜያት መሻሻል ያለባቸው ተግባራት ላይ አቅጣጫ በመስጠት የግምገማ መድረኩ ተጠናቋል።