የግብርና ቆጠራ ቀሪ ተግባራት ላይ ውይይት ተደረገ

1t8a2269

ሐምሌ 2/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት እያካሄደ በሚገኘው የግብርና ቆጠራ አፈፃፀምና ቀጣይ ስራዎች ላይ ከባለድርሻ አካካት ጋር ውይይት  አደረገ። በውይይት መድረኩ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ የኢኮኖሚ ስታቲስቲክስ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ቀሬ  የግብርና ቆጠራን በሚመለከት ከቆጠራው ቅድመ ዝግጅት ተግባራት አሁን እስክደረሰበት የስራው አፈፃፀም ድረስ የባለድርሻ አካላት  ተሳትፎ ከፍተኛ ሚና እንዳለው አንስተው የዛሬው መድረክም ስራው የደረሰበትን አፈፃፀምና ቀጣይ ቀሪ ስራዎች ለመወያየት እንደሆነ  ገልፀዋል። የግብርና ቆጠራ አጠቃላይ ሂደትና የደረሰበትን አፈፃፀም የሚያሳይ ገለፃ የቀረበ ሲሆን በቀረበው ገለፃና በቀጣይ የበልግ፣ የንግድ እርሻዎች መረጃ መሰብሰብና የሪፖርት ዝግጅት ተግባራት ላይ ውይይት ተደርጎበታል። በመድረኩ የተገኙት ባለድርሻ አካላትም ቆጠራው ጥሩ  የሚባል አፈፃፀም ላይ መሆኑን ከቀረበው ሪፖርት መረዳታቸውን ተናግረዋል። በመድረኩ ማጠቃለያ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ በመድረኩ ለተገኙት ባለድርሻ አካላት ከቆጠራው ቅድመ ዝግጅት አሁን እስከደረሰበት አፈፃፀም ላደረጉት ተሳትፎ አመስግነው፤ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ በጋራ መስራት ውጤታማ እንደሚያደርግ በማንሳት ቀጣይ ቀሪ ስራዎችንም በጋራ እንደሚሰሩ ገልፀው  የውይይት መደረኩ ተጠናቋል።

የአስተዳደራዊ መዛግብት መረጃ አሰባሰብ፣ አያያዝና ትንተና ሂደቱን ለማሻሻል የሚያግዝ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

1t8a1994.jpg

  የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከአስተዳደራዊ መዛግብት የሚገኙ መረጃዎችን እንደኦፊሴላዊ ስታቲስቲክስ መረጃ ለመጠቀም  የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ለተውጣጡ አመራሮችና  ባለሙያዎች በክልሉ ዋና ከተማ ሰመራ እየተሰጠ ይገኛል። ስልጠናው ያስጀመሩት የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ አሊ መሀመድ በክልሉ የተለያዩ ሴክተር  መስሪያ ቤቶች የሚያመነጩትን የአስተዳደራዊ መረጃዎችን አሰባሰብ፣ አያያዝ፣አደረጃጀትና ትንተና ሂደቱን በማሻሻል እንደኦፊሴላዊ  ስታቲስቲክስ መረጃ ለመጠቀም ስለመረጃዎቹ አስፈላጊነትና ያላቸው ጠቀሜታ ላይ በቂ ግንዛቤና መሠረታዊ ዕውቀት ያለው አመራርና  ባለሙያ መፍጠር ቀዳሚ ተግባር እንደሆነ አንስተው ስልጠናው ከዚህ አንፃር የሚታያውን የሰው ሀይል የአቅም ክፍተቶችን በማሻሻል  ከክልሉ የተለያዩ ሴክተር መሠሪያ ቤቶች የሚያመነጩትን የአስተዳደራዊ መረጃዎችን ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕቅዶች ግብዓትነት  ለመጠቀም የሚያስችል የባለሙያዎችን አቅም ለመፍጠር የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን አስረድተው የስልጠናው ተሳታፊዎች ወደየሴክተር  መስሪያ ቤታቸው ሲመለሱ ያገኙትን እውቀትና ልምድ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚጠባቅበቸውም መልዕክታቸውን አሰተላልፈዋል። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስታቲስቲክስ ሜቶዶሎጂና ልማት ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬከተር ክብርት ወ/ሮ ጀሚላ መሀመድ ስልጠናው በየሴከተሩ ያለውን የአስተዳደራዊ መረጃ አያያዝ ለማሻሻል የሚረዱ የስታቲስቲክ ፅንሰ ሀሳብና የቴክኖሎጂ አጠቀቃም ላይ በየክልሉ የሚገኙትን ባለሙያዎች አቅም በማሳደግ ከአስተዳደራዊ መዛግብት የሚገኙትን መረጃዎችን ጥራት በማሻሻል  እንደአንድ ኦፊሴላዊ ስታቲስቲክስ መረጃ ለመጠቀም በተቋሙ ሪፎርም ትኩረት ተሰጥቶ በየክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙት ተግባራት አካል  እንደሆነ ገልፀዋል። ስልጠናው በአስተዳደር መረጃዎች አመዘጋገብ፣አያያዝና የቴክኖሎጂ አጠቀቃም ላይ ለቀጣይ ሶስት ቀናት እንደሚሰጥ ከስልጠናው  መርሀግብር ለመረዳት ተችሏል።

በዓመታዊ የስታቲስቲክስ መጽሄት ዝግጅት መነሻ ይዘት ላይ ውይይት ተካሄደ

aa3a8839

ሰኔ24/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከተለያዩ ጥናቶችና የአስተዳደር መዛግብት የተገኙትን መረጃዎች በማደረጃትና አስፈላጊውን የጥራት  ደረጃ በመከተል በሚያዘጋጀው ዓመታዊ የስታቲስቲክስ መጽሄት /statistical Abstract/ አካል በሆነው የ2016 ዓ.ም መፅሔት ዝግጅት መነሻ ይዘት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ። የውይይት መድረኩን ያስጀመሩት የተቋሙ የስነ-ህዝብ እና ማህበራዊ ስታቲስቲክስ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ አይናለም ተሻገር ተቋሙ ከኢኮኖሚያዊ እና ከማህበራዊ ጥናቶች እንዲሁም ከተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የአስተዳደር መዛግብትየሚገኙትን መረጃዎችን በማሰባሰብ፣ በመተንተንና በማደራጀት በተለያዩ ፎርማት አዘጋጅቶ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ ለማድረግ እያሰራ  እንደሚገኝ አንስተው የስታቲስቲክስ መጽሄት /statistical Abstract/ በርካታ መረጃዎችን በአንድ ፎርማት አካቶ የሚይዝ በመሆኑ፤ ለፖሊሲ፣ ለልማት ዕቅዶች ዝግጅት እና ግምገማና ክትትል እንዲሁም ለልዩ  ልዩ ምርምር ስራዎች እንደአንድ የመረጀ አማራጭ ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑን በማስረዳት፤ በዓመታዊ መጽሄት የሚካተቱ መረጃዎች  ጥራት እንዲኖራቸው ከቅድመ ዝግጅት ሂደት ጀምሮ የመረጃዎቹን ምንጭ ከሆኑት ባለድርሻ አካላት ጋራ በተዘጋጀው የመጽሄቱ መነሻ  ይዘት ዙሪያ ውይይት በማድረግ የሚገኙትን ተጨማሪ ግብዓቶችን ማካታት አስፈላጊ በመሆኑ የውይይቱ መድረኩ መዘጋጀቱን ገልፀው  ዓመታዊ መጽሄቱ በተቻለ መጠን የመረጃ ምንጭ የሆኑትን ተቋማት የመረጃ ፍላጎት ያማከለና ጥራቱ የተሟላ እንዲሆን ተሳታፊዎች  ያላቸውን ሀሳብ በመስጠት የበኩላቸውን ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል ። በውይይቱ የዓመታዊ የስታቲስቲክስ መጽሄት ዝግጅት መነሻ ይዘት ገለፃ በተቋሙ ማህበራዊ አካቶ ስታቲስቲክስ መሪ ስራ አስፈጻሚ  ከፍተኛ ባለሙያዎች ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን በመድረኩ የተነሱ ሀሳብና አስተያየቶች እንደግብዓት በመውሰድ የውይይት መደረኩ ተጠናቋል።

የመረጃ ጥራት ቁጥጥር አቅም ለማሳደግ የሚያስችል ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

aa3a8644

ሰኔ 17/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ተቋማዊ የመረጃ ጥራት ቁጥጥር አቅምን ለማሳደግ የሚያስችል ስልጠና ከተቋሙ የተለየዩ ስራ  ክፍሎች ለተወጣጡት ከፍተኛ ባለሙያዎች ከስታቲስቲክ ኖርዌይ በመጡ በዘርፋ የተሻለ ልምድና ዕውቀት ባካበቱ ባለሙያዎች እየተሰጠ ይገኛል። ስልጠናው ተቋሙ በስታቲስቲክስ መረጃ ጥራትና አቅርቦት ተወዳዳሪና በሂደትም የዘርፋ የልህቀት ማዕከል ለመሆን የጀመረውን ጉዞ  እውን ለማድረግ የሚያስፈልገውን የሰው ሀይል ለመፍጠር የጎላ ፋይዳ ያለው ሲሆን ስታቲስቲክ ኖርዌይ የተቋሙን የመረጃ ጥራት  ቁጥጥር አቅም ግንባታና ሌሎች የሪፎርም ተግባራት እንዲሳኩ እገዛ እያደረጉ ከሚገኙ አለም አቀፍ ባላድርሻ አካላት መካከል አንዱ ነው።

የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርዓት አጠቃቀም ላይ ስልጠና ተሰጠ

photo 2025 06 23 19 01 03 copy

ሰኔ 16/2017ዓ.ም፣ ሶዶ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርዓት (Integrated management system (IMIS)) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከሚገኙ 25 ሴክተሮች መስሪያ ቤቶች ለተወጣጡ ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ። ተቋሙ ከተለያየ ምንጭ የሚሰበስባቸውን የስታቲስክስ መረጃዎችን በሳይንሳዊ ዘዴ በመተንተን ሪፖርቶቹን ተደራሽ ለማድረግ ጥቅም ላይ ካዋላቸው ዲጂታል የመረጃ ስርጭት መሳሪያዎች መካከል አንዱ የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርዓት (Integrated management system (IMIS) ሲሆን የስርዓቱ አጠቃቀም ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየሰራ ይገኛል።  በዚሁ መነሻ ተቋሙ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮና ከክልሉ 25 ሴክተሮች ለተወጣጡ 100 ባለሙያዎች ስልጠና የሰጠ ሲሆን ተሳታፊዎቹ ወደ ስራ ቦታቸው ሲመለሱ ያገኙትን ልምድና ዕውቀት የመረጃ አጠቃቀም ስርዓት ተግባራዊ በማድረግ በክልሉ ለእቅድና ክትትል የስታቲስቲክስ መረጃን የመጠቀም ፍላጎትና ግንዛቤ በማሳደግ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልፀዋል።

የስርዓተ ፆታና የአካል ጉዳተኞች ስታቲስቲክስ መመሪያ ዝግጅት ላይ ውይይት ተደረገ

photo 3 2025 07 18 11 22 19

ሰኔ 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስርዓተ ፆታና የአካል ጉዳተኞች ስታቲስቲክስ መረጃዎችን በጥናት፣ በቆጠራና በአስተዳደራዊ  መዛግብት መረጃዎች ለማካተት የሚያስችል መመሪያ ላይ ከተቋሙ መሪ ስራ አስፈፃሚዎች ጋር ውይይት አደረገ። በውይይት መድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የስነ-ሕዝብና ማህበራዊ ስታቲስቲክስ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ አይናለም ተሻገር የስርዓተ ፆታና የአካል ጉዳተኞች ስታቲስቲክስ የመረጃ ክፍተት መኖሩን ገልፀው ፤ ተቋሙ በሚያዘጋጃቸው የጥናትና  ቆጠራ መረጃዎች ወጥና አለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የስርዓተ ፆታና የአካል ጉዳተኞች ስታቲስቲክስ መረጃዎች እንዲካተቱ ለማስቻል መመሪያው መዘጋጀቱን አንስተው ሁሉም ጥናትና ቆጠራ የሚያከናውኑ የስራ ክፍሎች ለመመሪያው ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦች እንዲሰጡ  የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል። የስርዓተ ፆታ፣ የአካል ጉዳተኝነት ስታቲስቲክስ መረጃዎችን ከጥናትና ቆጠራ በተጨማሪ ከሌሎች አማራጭ የመረጃ ምንጮች ከተቋማት፣ ከማህበረሰብ ክፍሎችና ከግለሰቦች ከሚሰበሰቡ መረጃዎች (citizen Generated data) ላይ ማግኘት እንደሚቻል ተጠቅሶ የተዘጋጁት መመሪያዎች በስራ ክፍሉ መሪ ስራ አስፈፃሚና ከፍተኛ ባለሙያዎች ቀርበው ውይይት  የተደረገባቸው ሲሆን ከተሳታፊዎች የተነሱ ሀሳብና አስተያየቶች እንደግብዓት ተወስደዋል። በመድረኩ ማጠቃለያ የስነ-ሕዝብና ማህበራዊ ስታቲስቲክስ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር  ወ/ሮ አይናለም ተሻገር የተነሱትን ሃሳብና አስተያየቶች በማካተት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተጨማሪ ውይይቶች  ተደርገው  መመሪያው  ስራ ላይ እንዲውል ቀጣይ የስራ አቅጣጫ በመስጠት ውይይቱ ተጠናቋል።

የሪፎርም ትግበራን በሚመለከት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

0002 1

ሰኔ 05/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የመንግስት አገልግሎት እና የአስተዳደር ሪፎርምን አስመልክቶ ለዋናው መስሪያ ቤት ሰራተኞች  የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ። ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የተቋሙ የስታቲስቲክስ ዲጂታላይዜሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሜሮን ክፈለው ተቋሙ መንግስት ያስቀመጠውን የሪፎርም ትግበራ ስራ አቅጣጫ ወደተግባር ለመቀየር የሚያስችሉ በርካታ ስራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን ገልጸው የዛሬው ስልጠና የዚሁ አካል እንደሆነና የተቋሙ የመንግስት አገልግሎት እና የአስተዳደር ሪፎርም ትግበራ ስራዎችን አስመልክቶ የተከናወኑ ተግባራትንና ቀጣይ ስራዎችን በተመለከተ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን ከስልጠናው በቂ  እውቀት በመያዝ ለተቋሙ የሪፎርም ስራዎች ስኬት የበኩላችሁን እንድታበረክቱ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመድረኩ በርካታ የሪፎርም ተግባራት ስራዎች አፈፃፀም በየደረጃው የቀረበ ሲሆን ከነዚህም መካከል የተቋሙ የሪፎርም ትግበራ  ደረጃዎች ዝርዝር ፣ ህግና ስርዓቶች፣አሰራርና አደረጃጀት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እና ሌሎች ርዕሶች ዙሪያ ተቋሙ በሪፎርም  እየተገበራቸው ያሉ ስራዎችን በተቋሙ አመራሮች እና ባለሞያዎች ሰፊ ገለጻ ቀርቦ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ስልጠናው  ተጠናቋል።

የኦዲት አሰራርና መረጃ አያያዝ ላይ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

aa3a8545.jpg

ሰኔ14/2017 ዓ.ም አዳማ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የኦዲት አሰራርን አስመልክቶ በተለያዩ ርዕሶች ላይ ከዋናው መስሪያ ቤት እና ከቅርንጫፍ ለተወጣጡ  የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡ ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የተቋሙ የዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብነት ሃዋዝ ባደረጉት ንግግር ስልጠናው በኦዲት አሰራርና መረጃ አያያዝ የሰራተኛውን ክህሎት ለማጎልበት፤ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ውሳኔ እንዲሰጡ ባለሙያዎችን ለማብቃት ፤የቴክኖሎጂ  አጠቃቀም ለማሳደግ የተዘጋጀ በመሆኑ ተገቢውን ትኩረት በመስጠት በንቃት በመሳተፍ በስልጠና የምታገኙትን ዕውቅት ተግባር ላይ እንድታውሉ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ስልጠናው ከፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች ለቀጣይ ሁለት ቀናት በተለያዩ ርዕሶች ላይ እንደሚሰጥ  ለማወቅ ተችሏል፡፡

የአስተዳደራዊ መረጃ አሰባበብ፣ አያያዝና ትንተና ለማሻሻል የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ

aa3a7653 001

ሰኔ5/2017ዓ.ም ሀዋሳ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የአስተዳደራዊ መረጃ አመዘጋገብ፣ አያያዝና ትንተና ለማሻሻል የሚያስችል ስልጠና ለሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕላንና ልማት ቢሮ ሀላፊዎችና ባለሙያዎች ሰጠ። በስልጠናውን መክፈቻ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስታቲስቲክስ ልማትና ሜቶዶሎጂ ዘርፍ  ምክትል ዋና ዳይሬክተር  ወ/ሮ ጀሚላ መሀመድ የአስተዳደራዊ መዛግብት መረጃዎች ለስታቲስቲክስ መረጃ ግብዓት መሆናቸውን አንስተው እንደሀገር ያሉትን  የመረጃ ክፍተቶች ለመሙላትና የክልሎችን አካውንት ለማዘጋጀት አስተዳደራዊ መረጃዎች ለኦፊሴላዊ ስታቲስቲክስ […]