ተቋማቱ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር አካሄዱ

ሐምሌ 24/2017ዓ.ም ለገጣፎ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 700 ሚሊየን የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በሸገር ከተማ በለገዳዲ ለገጣፎ ክፍለ ከተማ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አካሄዱ። መርሀ ግብሩን በንግግር ያስጀመሩት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ጥሩማር አባተ በሀገራችን የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር መካሄድ ከጀመረበት ጊዜ […]
የ2017ዓ.ም አረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ተካሄደ

ሐምሌ 17/2017ዓ.ም አዳማ፣የፕላንና ልማት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል የ2017 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር በምስራቅ ሸዋ ሎሜ ወረዳ የችግኝ ተከላ አካሄዱ። መርሀግብሩን ያስጀመሩት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ጥሩማር አባተ በባለፉት ሰባት ዓመታት በክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ አመራር ሰጪነት የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻራ የማኖር ዘመቻ ስራ ሳይቆራረጥ […]
በ2017 በጀት ዓመት ተቋሙ የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገቡ ተገለፀ

ሐምሌ 16/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በመካከለኛ ዘመን (ከ2016-2018ዓ.ም) በስታቲስቲክስ ልማት ዕቅድ ለማሳካት ከታቀዱት አራት ትላልቅ ተግባራት ሶስቱን ተግባራዊ በማድረግ የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገቡን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ገለፀ። በ2017 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀምና 2018 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ለመወያየት የፕላንና ልማት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በተገኙበት መድረክ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት (ከ2016-2018ዓ.ም) ለማሳካት ካቀዳቸው ተግባራት መካከል የኢትዮጵያ ስነ-ህዝብና ጤና […]
በ2018 የሀገራዊ ልማት እቅድ ላይ ውይይት ተደረገ

ሐምሌ 16/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በ2018ዓ.ም ሀገራዊ የልማት እቅድ ላይ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች ጋር ውይይት ተደረገ። የውይይት መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ጥሩማር አባተ በሀገራችን በ2017 በጀት ዓመት በሁሉም ዘርፎች የተሻለ ውጤት የተመዘገበበት ዓመት መሆኑን አንስተው በ2018 በጀት ዓመት ቀጣይነት ያለው እድገት […]
ተቋማቱ በጋራ መስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ

ሐምሌ 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በዓለም ባንክ ድጋፍ በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር በገጠር መንገድ ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮጀክት የሚሰሩትን የገጠር መንገድ ግንባታ ስራዎች መሰራታቸውን ለማረጋገጥ (Verification) የሚያስችል ስራ ለመስራት ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር ስምምነት ተፈራረመ። የስምምነት ሰነዱን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ የትምጌታ አስራት እና የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና […]
የ2018 የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የቅድመ አሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

ሐምሌ 9/2017ዓ.ም አዳማ ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አግልግሎት በ2018ዓ.ም ለሚያካሄደው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የቅድመ አሰልጣኞች ስልጠና ከዋና መሠሪያ ቤትና 26ቱ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለተወጣጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች እየተሰጠ ይገኛል። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2018ዓ.ም የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ለማካሄድ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እያከናወነ መሆኑን አንስተው ከነዚህ የቅድመ ዝግጅት ተግባር መካከል አንዱ […]
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የቅድመ ዝግጅት ስራ ተጀመረ

ሐምሌ 8/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2018ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ለሚካሄደው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የቅድመ ዝግጅት ስራ መጀመሩን በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት በተጋጀው የማስጀመሪያ ፕሮግራም ይፋ አደረገ። በቅድመ ዝግጅት ተግባራት የቆጠራው ስነ ዘዴ፣ የሰው ሀይል ዝግጅት፣ ለመስክ ስራ የሚውሉ ግብዓቶችና የቴክኖሎጂ ዝግጅት በዋናነት እንደሚከናወኑ የተገለፀ ሲሆን ይህን ስራ የሚያስተባብር ኮሚቴ ከዛሬ ጀምሮ እነዚህን ስራዎች […]
የስራ አፈፃፀም ግምገማ ተጠናቀቀ

ሐምሌ 5/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች፣ ዋና መስሪያ ቤትና የ26ቱ ቅርንጫፍ ጽህፈት ኃላፊዎች በተገኙበት እየተካሄደ የሚገኛው የ2017 ዓ.ም የተቋሙ ስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ሁለተኛ ቀን ውሎ በ2018ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጀ ለመጀመሪያ የሚካሄደው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ መሪ ዕቅድ ገለፃ በቢዝነስ ስታቲስቲክስ መሪ ስራ አስፈፃሚ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። በግምገማ መድረኩ ማጠቃለያ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ በ2017 ዓ.ም ስራ አፈፃፀም የተገኙትን ጠንካራ ተሞክሮዎችን አጠናክሮ በመቀጠልና የታዩትን ክፍተቶች በመፍታት በ2018ዓ.ም የተቋሙ ስራ ዕቅድ የሚከናዋኑ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ፣ የስነ-ሕዝብና ጤና ጥናት፣ ብሔራዊ የተቀናጀ የቤተሰብ ጥናትና የግብርና ቆጠራ ውጤት ሪፖርት ዝግጅት ተግባራትን በተሟላ መልኩ ለመሳካት በየደረጃው የሚገኘው የተቋሙ አመራርና መላው ሠራተኞች በቂ ዝግጅት ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ቀጣይ የስራ አቅጣጫ በመስጠት የግምገማ መድረኩ ተጠናቋል።
ለተቋሙ የቀድሞ አመራር የሽኝት ፕሮግራም ተደረገ

ሐምሌ 5/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከጥቅምት 18/2015ዓ.ም እስከ ሰኔ 27/2017ዓ.ም ድረስ በኢኮኖሚ ስታቲስቲክስ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው ሲያገለግሉ ለቆዩትና ከሰኔ 25/2017ዓ.ም ጀምሮ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ለተሾሙት አቶ ሙሉቀን ቀሬ በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት የሽኝት ፕሮግራም ተደረገ። በተቋሙ ከፍተኛ አመራርና ሠራተኞች በተዘጋጀ የሽኝት ፕሮግራም ላይ የተገኙት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ በረከት ፍስሀ ፅዮንና የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ክቡር አቶ ሙሉቀን ቀሬ በተቋሙ ቆይታቸው ለሰጡት የላቀ አመራርና ላሳዩት ትጋት ምስጋናቸውን አቅርበው ቀጣይ የስራ ጊዜያቸው የተሳካ እንዲሆን ምኞታቸውን ገልፀዋል።
የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ተደረገ

ሐምሌ 4/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2017በጀት ዓመት ያካሄዳቸው የጥናቶችና የቆጠራ ስራዎች አፈፃፀም ሪፖርት የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ፣የዋናው መስሪያ ቤት እና የቅርንጫፍጽህፈት ቤት የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት ተገመገመ። መድረኩን ያስጀመሩት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ተቋማችን በ2017 በጀት ዓመት ያከናወናቸውን የግብርና ቆጠራ፣ የስነ-ህዝብና ጤና ጥናትና ብሔራዊ የተቀናጀ የቤተሰብ ጥናት ሪፖርት ስንገመግም በሂደቱ የተገኙ ጥሩ ልምዶች፣ ያጋጠሙ ችግሮችና በቀጣይ ትኩረት የሚፈልጉ ጉዳዮች በውይይቱ ተነስተው ልንማርባቸው እንደሚገባ አንስተው በስራው እስከአሁን በተገኘው ውጤት በከፍተኛ ትጋትና መነሳሳት ለሰሩ መላው የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች እንዲሁም በዚህ ሂደት ውስጥ እገዛ ላደረጉ ሁሉም ባለደርሻ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በበጀት ዓመቱ ሲከናወኑ የነበሩ የስነሕዝብና ጤና ጥናት፣ ብሔራዊ የተቀናጀ የቤተሰብ ጥናትና የግብርና ቆጠራ የደረሱበትን የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ገለፃ ቀርቦ ቀርቦ ሰፊ ውይይት የተደረገበት ሲሆን በነገው ዕለትም የውይይት መድረኩ ይቀጥላል።