ተቋማቱ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ

ግንቦት 14/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በሀገራችን በምርምርና ልማት ዘርፍ ያለውን የመረጃ ክፍተት የሚሞላ ብሔራዊ የምርምርና ልማት ጥናት በጋራ ለማካሄድ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ። ስምምነቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ እና የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በከር ሻሌ በጋራ ፈርመውታል። የጥናቱ ዋና ዓላማ የምርምርና ልማት ወጪን ከሀገር […]
”የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነፃነት” በሚል መሪ ቃል ላለፋት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ሀገራዊ ጉባኤ ተጠናቀቀ

ግንቦት 12/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ በፕላንና ልማት ሚኒስቴርና በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ሀገራዊ ጉባኤ መጠናቀቁ ተገለፀ። በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ በረከት ፍስሀፅዮንና የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል። ለሶስት ቀናት የተዘጋጀው ሀገራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ አንፃር የተሰሩ ስራዎችና […]
‘’የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነፃነት’’ በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ሀገራዊ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል

ግንቦት 10/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ ‘’የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነፃነት ‘’ በሚል በፕላንና ልማት ሚኒስቴርና በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በጋራ የተዘጋጀ ሀገራዊ ጉባኤ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ክቡር ዶ/ር ዐብይ አህመድን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል። መረጃ ሀገራዊ ራዕያችን የሆነውን ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት፣ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ዋነኛ ግብዓት መሆኑን አንስተው ይህን መረጃ በሀገር ባለሙያዎች ዕውቀትና […]
በተቋሙ በተዘጋጀው የዕውቀት ግብይት መድረክ ላይ ነባር ዕውቀቶች ቀርበው ግንዛቤ ተፈጥሮበታል

ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ በተቋሙ ዋና መሥሪያ ቤት ለሶስተኛ ጊዜ የዕውቀት ሽግግር መድረክ ተዘጋጅቶ የግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ ተሠርቷል። የተቋሙ የስታቲስቲክስ መረጃ ስርጭት እና ተደራሽነት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ትግስት በቀለ በተቋሙ ውስጥ የሚገኙ ሁሉም የሥራ ክፍሎች ማንኛውንም ዕውቀት በአግባቡ መሰነድ እንዳለባቸው አንስተው፣ የዕውቀት ሽግግር የተቋሙ ባህል በማድረግ፣ ዕውቀትን መለዋወጥ እና ለተተኪ ትውልድ በተደራጀ መልኩ […]
የሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞችን መረጃ የማረጋገጥ የመስክ ስራ ለሚያስተባብሩ ባለሙያዎች የስራ ስምሪት ተሰጠ

ሚያዚያ 26/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎትና ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ለሚያካሂደው የመንግስት ሰራተኞች መረጃ የማረጋገጥ የመስክ ስራ ለሚያስተባብሩ ከዋናው መ/ቤት ወደ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለሚሄዱ ባለሙያዎች የስራ ስምሪት ተሰጠ። በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የተቋሙ የስነ ሕዝብና ማህበራዊ ስታቲስቲክስ ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ አይናለም ተሻገር የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ለማረጋገጥ ስራ የሚያስፈልገውን ስልጠና ተጠናቆ […]
ለተቋሙ ሰራተኞች በሰው ኃይል መረጃ ማረጋገጥ ስራ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ ግብር ተካሄደ

ሚያዝያ 22/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎትና ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ለሚያካሂደው የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ማረጋገጥ ስራ ላይ ለተቋሙ ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ ግብር ተካሄደ። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የብቃትና የሰው ሀብት አስተዳደር ስራ አስፈፃሚ አቶ አወል አባመጫ የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ማረጋገጥ ስራውን ለመጀመር የቅድመ ዝግጅት ተግባር መጠናቀቁን እና ተቋማችንም አንዱ የዚሁ አካል በመሆኑ […]
የተቋሙ የዘጠኝ ወር እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተደረገ

ሚያዚያ 15/2018 ዓ.ም አዲስ አበባየኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት ያከናወናቸውን ተግባራት አፈፃፀም የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዋና መ/ቤትና የ26ቱ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች በተገኙበት መድረክ ተገመገመ። የግምገማ መድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የኢ.ስ.አ (ከ2016-2018) በመካከለኛ ዘመን የስታቲስቲክስ ልማት እቅድ የታቀዱትን ቆጠራና ጥናቶች በስኬት ማጠናቀቁን አንስተው በ2018 በጀት […]
የመንግስት ሰራተኞች ፐርሶኔል መረጃ የማረጋገጥ የመረጃ ሰብሳቢዎችና ተቆጣጣሪዎች ስልጠና መስጠት ተጀመረ

ሚያዚያ 7/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር በጋራ ለሚካሂደው የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ለማረጋገጥ ለሚሰማሩ መረጃ ሰብሳቢዎችና ተቆጣጣሪዎች በሀገሪቱ በተዘጋጁ 9 የስልጠና ማዕከላት መሰጠት ተጀመረ። ስልጠናውን ከማዕከል በበይነ መረብ ያስጀመሩት የተቋሙ ዋና ዳ/ር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለመችውን ብልፅግና እውን ለማድረግ ከነደፈቻቸው ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች አንዱ የልማት አቅም […]
የመንግስት ሰራተኞችን ፐርሶኔል መረጃ ለማረጋገጥ ለሚሰማሩ የስልጠና አስተባባሪዎች ኦረንቴሽንና የስራ ስምሪት ተሰጠ

ሚያዚያ 5/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ለሚያካሂደው የመንግስት ሰራተኞችን ፐርሶኔል መረጃ ለማረጋገጥ በመረጃ ሰብሳቢዎችና ተቆጣጣሪዎች ስልጠና ለሚሰማሩ ከዋናው መ/ቤትና ከሲቪል ሰርቪስ ለተውጣጡ የቴክኒክና የሎጂስቲክ አስተባባሪዎች ኦረንቴሽንና የስራ ስምሪት ተሰጠ። በመድረኩ የተገኙት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ተቋሙ ከዚህ ቀደም ትላልቅ ሀገራዊ ቆጠራዎችና ጥናቶችን በስኬት ማከናወኑን አንስተው […]
በተቋሙ ለተከናወኑ የህንፃ ሪኢኖቬሽን ስራዎች እውቅና ተሰጠ

መጋቢት 29/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከፍተኛ አመራሮች በተቋሙ ዋና መ/ቤት በተከናወኑ የህንፃ ጥገና፣ ግንባታና ሪኢኖቬሽን ስራዎች ለኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን እውቅና የመስጠት መርሃ ግብር አካሄደ። በመርሀ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ተቋሙ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ የሪፎርም ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን አንስተው በሪፎርም ተግባሩ የትኩረት አቅጣጫ […]