ለኮሪያ ስታቲስቲክስ ልዑካን ቡድን ስለተቋሙ ገለጻ ተደረገ

ነሐሴ 5/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ለኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመስጠት ወደ ኢትዮጵያ ለመጡት የኮሪያ ስታቲስቲክስ ልዑካን ቡድን ስለተቋሙ ግንዛቤ ማስጨበጫ ገለጻ ተደረገ። የልዑክ ቡድኑን ለመቀበል በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ተገኝተው የተቋሙ ከምስረታው ጀምሮ አሁን እስከ ደረሰበት ደረጀ ያለፈባቸውን ተቋማዊ ጉዞ፣ በሂደቱም የተገኙ ውጤቶች እና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጨ ላይ ገለፃ ያቀረቡት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስታቲስቲክስ […]
የኮሪያ ስታቲስቲክስ ለተቋሙ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል

ነሐሴ 5/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፣የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎትና ኮሪያ ስታቲስቲክስ በሰው ሀይል አቅም ግንባታ ላይ በትብብር ለመስራት ከዚህ ቀደም የተፈራረሙት የጋራ ስምምነት አካል የሆነውን የአቅም ግንባታ ስልጠና ከኮሪያ ስታቲስቲክስ በመጡት ባለሙያዎች በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት መሰጠት ተጀመረ። በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ ተገኝተው ስልጠናውን ያስጀመሩት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ባከር ሻሌ ኢትዮጵያና ኮሪያ ያላቸው ግንኙነት ከልማት […]
ለሁለተኛ ዙር የአሰልጣኞች ስልጠና አስተባባሪዎች የስራ መመሪያ ተሰጠ

ነሐሴ 2/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2018ዓ.ም ለሚካሄደው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በ13 የስልጠና ማዕከላት ከነሐሴ 7/2017ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጠውን የአሰልጣኞች ስልጠና ለማስተባበር ከዋናው መስሪያ ቤት ወደ ማዕከላቱ ለተመደቡት 80 ባለሙያዎች የስራ መመሪያ ተሰጠ። በመድረኩ ላይ የተገኙት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በከር ሻሌ በ2017ዓ.ም በተሰሩት ትላልቅ ሀገራዊ ጥናቶችና ቆጠራ የተገኙትን መልካም ተሞክሮዎች በማስቀጠል እንደክፍተት የታዩትን […]
ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደረገ

ነሐሴ 1/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣በ2018ዓ.ም በሚያካሄደው የግብርና ናሙና ጥናትና ላይ ከብሔራዊ ቲክኒካል ኮሚቴ ጋር ውይይት ተደረገ።የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ዓመታዊ የግብርና ናሙና ጥናት የግብርና ቆጠራ በተካሄደበት ማግስት መካሄዱ በቆጠራው የተገኙ ግብዓቶችን በማካተት ጥራት ያለው የግብርና ናሙና ጥናት ለማከናወን እንደሚያግዝ ገልፀው፤የውይይት መድረኩ የተዘጋጀው ከባለድርሻ አካላት ጋር በመወያየት የሚነሱ አስተያየቶችን እንደግብዓት ለመጠቀም ታስቦ መሆኑን ገልፀዋል። […]
የተቋሙ የዕውቀት ካፌ የማስተዋወቅ ፕሮግራም ተካሄደ

ሐምሌ 30/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ተቋማዊ እውቀትን ለማጋራት የሚያስችል የዕውቀት ካፌ የማስተዋወቅ ፕሮግራም ተካሄደ።ፕሮግራሙን በንግግር ያስጀመሩት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስታቲስቲክስ ዲጂታላይዜሽን ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሜሮን ክፈለው የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በተቋማዊ ሪፎርሙ ትኩረት ሰጥቶ በማከናወን ከሚገኘው ተግባራት ውስጥ አንዱ የዕውቀት አስተዳደር ስርዓትን መገንባት አገልግሎት ላይ ማዋል ሲሆን በዛሬው ዕለት የምናስተዋውቀው የዕውቀት ካፌ (knowledge cafe) […]
የዓለም አቀፍ ስነ-ሕዝብ ፈንድ (UNFPA) ለተቋሙ ድጋፍ አደረገ

ሐምሌ 29/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ የዓለም አቀፍ ስነ-ሕዝብ ፈንድ የኢትዮጵያ ቫይታል ስታቲስቲክስ መረጃ አሰባሰብና ሲቪል ምዝገባ ስርዓትን ለማዘመን እየተከናወኑ የሚገኙትን የሪፎርም ስራዎችን ለማጠናከር የሚያግዙ 17 ዴስክቶፕ ኮምፒውተሮች ድጋፍ ለኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አስረከበ። በርክክብ መርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የኢትዮጵያ መንግስት ዜጎች ከልደት እስከ ሞት የሚኖራቸውን መረጃ በአግባቡ በመሰብሰብ፣ በማደራጀትና […]
በ2018 ዓ.ም ለሚካሄደው የግብርና ናሙና ጥናት የአሰልጣኞች ስልጠና ተጀመረ

ሐምሌ 28/2017ዓ.ም አዳማ፣የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየዓመቱ ከሚያካሂዳቸው የናሙና ጥናቶች አንዱ የሆነውን የ2018ዓ.ም ግብርና ናሙና ጥናት የመስክ ስራ የሚሰሩትን መረጃ ሰብሳቢዎች የሚያሰለጥኑ አሰልጣኞች ስልጠና መሰጠት ተጀመረ። በስልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የ2018ዓ.ም የግብርና ናሙና ጥናትን ከሁለተኛ ዙር ሀገር አቀፍ የግብርና ቆጠራ የመስክ ስራ በሚጠናቀቅበት ማግስት ማካሄድ ያስፈለገው በጥናቱ […]
ከፍተኛ አመራሩ ለክልሉ አመራር የስታቲስቲክስ ልማት ፕሮግራም እንዲሳካ የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበ

የሲዳማ ብሔራዊ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ ደስታ ሌዳሞ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በስታቲስቲክስ ልማት ዕቅድ ፕሮግራም እያከናወናቸው በሚገኙ ቆጠራዎችና ጥናቶች ላይ ለስራው መሳካት በሲዳማ ክልል ከሚገኘው የሀዋሳ ስታቲስቲክስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ጋር በቅርበት በመደገፍ ለሀገራዊ ስታቲስቲክስ ቆጠራዎች እና ጥናቶች መሳካት ምቹ ሁኔታዎች እንደሚፈጥሩ ገልፀዋል:: በ2017ዓ.ም በክልሉ ውስጥ የተከናወኑ ተግባራትም ውጤታማ እንደነበሩ እና የክልሉ ድጋፍ አዎንታዊ […]
የፕላንና ልማት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የክረምት በጎ አድራጎት ስራ አስጀመሩ

ሐምሌ 26/2017ዓ.ም፣የፕላንና ልማት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በሲዳማ ክልላዊ መንግስት ደቡብ ሲዳማ ዞን ዳራ ወረዳ መጬሾ የገጠር ቀበሌ በመገኘት የ2017ዓ.ም የክረምት በጎ አድራጎት ስራ አስጀመሩ። በገጠረ ቀበሌው ተገኝተው የክረምት በጎ አድራጎት ስራውን ያስጀመሩት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ጥሩማር አባተ የዚህ ዓመት የበጎ አድራጎት ስራ ባለፋት ዓመታት ከተሰሩት በተለየ መልኩ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር […]
ለተቋሙ ከፍተኛ አመራር ደማቅ አቀባበል ተደረገ

ሐምሌ 25/2017ዓ.ም ሀዋሳ፣የ2017 ዓ.ም የክረምት በጎ አድራጎት ተግባራት ለማከናዋን ወደ ሲዳማ ክልል ለተጓዘው የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከፍተኛ አመራር የሲዳማ ክልል የፕላንና ልማት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር አራርሶ ገረመውና በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የሀዋሳ ስታቲስቲክስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አሰጋሽ አሰፋ በሀዋሳ አየር ማረፊያ ተገኝተው ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ከፍተኛ አመራሩ ነገ ሐምሌ 26/2017ዓ.ም በሲዳማ ክልል ደቡባዊ […]