
ግንቦት 25/2017ዓ.ም አዳማ፣
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ሴቶችን ለማብቃት የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና ከተቋሙ ዋና መስሪያ ቤትና ከቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለተውጣጡ ባለሙያዎች ሰጠ።


የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብነት ሀዋዝ እንደተቋም ሴቶችን ማብቃትና ወደ አመራር ማምጣት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራበት መሆኑን አንስተው የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በሰራው ሪፎርም ሴቶችን ወደ አመራር በማምጣት ሌሎች ባለሙያዎችንም ለማብቃት እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል።
ስልጠናውን በስርዓተ ፆታ፣ የማካተት ፅንሰ ሀሳብ አስፈላጊነት፣ ስልቶች፣ ተግዳሮቶችና ልዩ ትኩረት የሚፈልጉ የማህበረሰብ ክፍሎች ፍላጎቶች ላይ ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በመጡት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ጌታቸው ካሴ እየተሰጠ ይገኛል።

ስልጠናው ከተለያዩ የስራ ክፍል ለተውጣጡ 45 ባለሙያዎች ለቀጣይ ሶስት ቀናት እንደሚሰጥ ከወጣው መርሀግብር ለመረዳት ተችሏል።