የመረጃ ጥራት ቁጥጥር አቅም ለማሳደግ የሚያስችል ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

ሰኔ 17/2017ዓ.ም አዲስ አበባ፣

aa3a8647

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ተቋማዊ የመረጃ ጥራት ቁጥጥር አቅምን ለማሳደግ የሚያስችል ስልጠና ከተቋሙ የተለየዩ ስራ  ክፍሎች ለተወጣጡት ከፍተኛ ባለሙያዎች ከስታቲስቲክ ኖርዌይ በመጡ በዘርፋ የተሻለ ልምድና ዕውቀት ባካበቱ ባለሙያዎች እየተሰጠ ይገኛል።

aa3a8629

ስልጠናው ተቋሙ በስታቲስቲክስ መረጃ ጥራትና አቅርቦት ተወዳዳሪና በሂደትም የዘርፋ የልህቀት ማዕከል ለመሆን የጀመረውን ጉዞ  እውን ለማድረግ የሚያስፈልገውን የሰው ሀይል ለመፍጠር የጎላ ፋይዳ ያለው ሲሆን ስታቲስቲክ ኖርዌይ የተቋሙን የመረጃ ጥራት  ቁጥጥር አቅም ግንባታና ሌሎች የሪፎርም ተግባራት እንዲሳኩ እገዛ እያደረጉ ከሚገኙ አለም አቀፍ ባላድርሻ አካላት መካከል አንዱ ነው።

aa3a8633
aa3a8637