የተቋሙ ሴት ሰራተኞች የስራ ላይ ብቃትና ክህሎት ለማሻሻል የሚያግዝ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

ታህሳስ 01/2018 ዓ.ም አዳማ

1t8a6624

ከኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና መስሪያ ቤት ከተለየዩ የስራ ክፍል ለተወጣጡት ሴት ሰራተኞች የስራ ላይ ብቃትና ክህሎት ለማሻሻል የሚያግዝ ስልጠና በአዳማ ከተማ እየተሰጠ ይገኛል።

1t8a6594

የተቋሙ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካትቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አዚዛ እስማኤል የተቋሙን ሴት ሰራተኞች ስራን የመፈጸም ብቃትና ክህሎት ለማሳደግ የሚያግዙ የስራ ላይ ስልጠናዎችን በማዘጋጀትና ተግባራዊ በማድረግ የተቋሙ ሴት ሰራተኞች በተሰማሩበት የስራ መስክ ውጤታማ እንዲሆኑ የስራ ክፍላቸው አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝ አንስተው ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥሉት ሶስት ቀናት የሚሰጠው ስልጠናም ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።

1t8a6631

በመድረኩ ተገኝተው ስልጠናውን ያስጀመሩት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብነት ሐዋዝ ተቋሙ ባለፋት ሶስት ዓመታት ተግባራዊ እያደረገ በሚገኘው ተቋማዊ ሪፎርም አንዱና ዋነኛው ትኩረት የሰው ሀይልን የመፈፀም ብቃትና ክህሎት ቀጣይነት ባለው መልኩ ማሻሻል እንደሆነ ገልፀው በተለይም የተቋሙን ሴት ሰራተኞች ሁለንተናዊ የመፈጸም አቅማቸውን በማሳደግ ወደ አመራርነት እንዲመጡ እየተሠራ መሆኑን በማስረዳት ሰልጣኞች ስልጠናውን በትኩረት በመከታተል ለቀጣይ ስራቸው የሚያግዛቸውን ዕውቀትና ክህሎት መቅሰም እንዳለባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

1t8a6634

ስልጠናው ለሚቀጥሉት ሶስት ቀናት በተለያዩ ርዕሶች ላይ ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች ይሰጣል።

1t8a6637
1t8a6641