በተቋሙ የሴቶች ቀን ”50 ዓመት የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለፀገች ኢትዮጵያ ” በሚል መሪ ቃል ተከበረ

t8a9961

መጋቢት 4/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የሴቶች ቀንን “50 ዓመት የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለፀገች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ተከበረ።

t8a9944

በበዓሉ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ የስነ-ህዝብና ማህበራዊ ስታቲስቲክስ ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ዓይናለም ተሻገር የሴቶች ቀን ስናከብር ከመብት ጥያቄ ባለፈ የእውቀት ነፃነት፣ ለተቋም ለውጥ ትልቅ ተምሳሌት ነው ያሉ ሲሆን እንደተቋምም ሴቶችን ወደአመራር ከማምጣት አንፃርና የመካከለኛ ዘመን እቅድ ስራዎችን በስኬት እያጠናቀቅንበት ያለንበት ወቅት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ሲሉ ገልፀዋል።

t8a9987

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አዚዛ እስማኤል በዓሉን ማክበር ያስፈለገበት ዋና ዓላማ ሴቶች በሀገሪቱ በሚካሄደው ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የሚኖራቸው የላቀ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት እንዲሁም በተለይ የኢኮኖሚ ውስንነት፣ ፆታን መሰረት ያደረገ ጥቃትን ለማስቆም ነው ሲሉ ገልፀዋል።

t8a9984

በዕለቱ በዓሉን በማስመልከት የተዘጋጀ አጭር ተውኔትና የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄዷል።

t8a9990
t8a9981
t8a0031
t8a0019