የተቋሙ የዘጠኝ ወር እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተደረገ

a3a1267

ሚያዚያ 15/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት ያከናወናቸውን ተግባራት አፈፃፀም የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዋና መ/ቤትና የ26ቱ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች በተገኙበት መድረክ ተገመገመ።

a3a1269
a3a1263


የግምገማ መድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የኢ.ስ.አ (ከ2016-2018) በመካከለኛ ዘመን የስታቲስቲክስ ልማት እቅድ የታቀዱትን ቆጠራና ጥናቶች በስኬት ማጠናቀቁን አንስተው በ2018 በጀት ዓመት በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ የተከናወነው የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በሁለት ዙር ከመስክ መረጃ የመሰብሰብ ተግባሩ በስኬት መጠናቀቁን ገልፀው በቀጣይም የቀሩ የመረጃ ማጥራትና ሪፖርት ስራዎችን በጋራ እናጠናቅቃለን ሲሉ ገልፀዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አክለው ለዚህ ስራ መሳካት አስተዋኦ ላደርጉ የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች፣ የስራ ኃላፊዎች፣ በስራው ለተሳተፉ መላው ሰራተኛ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

a3a1298
a3a1448


በመድረኩ የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሪፖርት በስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ አቶ ሁሴን አጎናፍር የቀረበ ሲሆን የተቋሙ የ2018 በጀት ዓመት የፊዚካል እቅድ አፈፃፀም 92.1% በመቶ መሆኑን በሪፖርቱ ተገልጿል።

a3a1443
a3a1455
a3a1447


በተጨማሪም በመድረኩ የግብርና ቆጠራ፣ የኢኮኖሚ ድርጀቶች ቆጠራ አፈፃፀምና በአሁኑ ሰዓት ለማካሄድ የቅድመ ዝግጅት ተግባር እየተደረገበት በሚገኘው የመንግስት ሰራተኞች ፐርሶኔል መረጃ የማረጋገጥ ስራ ላይ ገለፃ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን በገለፃው ላይ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች በዋና ዳይሬክተር ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸው የግምገማ መድረኩ ተጠናቋል።

a3a1399
a3a1407
a3a1422
a3a1430