የስራ ፈጠራ፣ የደንበኞች አገልግሎትና አያያዝ ለማሻሻል የሚያስችል ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

መጋቢት 24/2018 ዓ.ም ፣

a3a0225

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስራ ፈጠራ፣ የደንበኞች አገልግሎትና የጊዜ አጠቃቀም ለማሳደግ የሚያስችል ስልጠና ድጋፍ ለሚሰጡ ሰራተኞች እየሰጠ ይገኛል።

a3a0263
a3a0288

በመድረኩ ተገኝተው ስልጠናውን ያስጀመሩት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብነት ሐዋዝ ተቋሙ ባለፋት ሶስት ዓመታት ተግባራዊ እያደረገ በሚገኘው ተቋማዊ ሪፎርም አንዱና ዋነኛው ትኩረት የሰው ሀይልን የመፈፀም ብቃትና ክህሎት ቀጣይነት ባለው መልኩ ማሻሻል እንደሆነ አንስተው የዛሬው ስልጠናም የስራ ፈጠራ፣ የጊዜ አጠቃቀም፣ የደንበኞች አገልግሎት አሰጣጥ፣ አዳዲስ አሰራሮችና መፍትሄዎች ማምጣት ላይ ትኩረቱን አድርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።

a3a0233

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አዚዛ እስማኤል በተቋሙ በምታከናውኗቸው የዕለት ተዕለት ተግባራት የተቋማችንን ግቦች ለማሳካትና የስራ ፈጠራን በማሳደግ በግል ህይወታችሁም ላይ ለውጥ እንድታመጡ ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና በመሆኑ ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ተግባር ላይ እንድታውሉ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

a3a0272

ስልጠናው ከኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ በመጡት ዶ/ር አወቀ አሸናፊ በስራ ፈጠራ፣ የደንበኞች አገልግሎትና አያያዝ እንዲሁም የጊዜ አጠቃቀምና ሌሎች ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ለቀጣይ አምስት ቀናት እንደሚሰጥ ከወጣው መርሀ ግብር ለመረዳት ተችሏል።