የመንግስት ሰራተኞች ፐርሶኔል መረጃ የማረጋገጥ የመረጃ ሰብሳቢዎችና ተቆጣጣሪዎች ስልጠና መስጠት ተጀመረ

a3a0898

ሚያዚያ 7/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር በጋራ ለሚካሂደው የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ለማረጋገጥ ለሚሰማሩ መረጃ ሰብሳቢዎችና ተቆጣጣሪዎች በሀገሪቱ በተዘጋጁ 9 የስልጠና ማዕከላት መሰጠት ተጀመረ።

a3a0912
a3a0952

ስልጠናውን ከማዕከል በበይነ መረብ ያስጀመሩት የተቋሙ ዋና ዳ/ር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለመችውን ብልፅግና እውን ለማድረግ ከነደፈቻቸው ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች አንዱ የልማት አቅም የሆነውን የሀገሪቷ የሲቪል ሰርቪስ ተቋምና አስፈፃሚዎችን ማዘመን፣ ብቃትና ስነ ምግባር ማነፅ እንዲሁም የማስፈፀም አቅም ማሳደግ አንዱ የሪፎርም አካል ነው ያሉ ሲሆን የተረጋገጠና ጥራት ያለው የሲቪል ሰርቪስ መረጃ መኖሩ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም በዚህ ስልጠና የምትሳተፉ መረጃ ሰብሳቢዎችና ተቆጣጣሪዎች ተልዕኮውን በሚገባ በመረዳትና ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል፣ በቂ ዕውቀትና ክህሎት በመጨበጥና በቡድን በመስራት ስራው የተሳካ እንዲሆን ሀገራዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

a3a0962
a3a0956

በበይነ መረብ ንግግር ያደረጉት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ ተቋማቸው ይህን ስራ ለማሳካት ከኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ጋር በቂ ቅድመ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን አንስተው፤ ስራው ዘመን ተሻጋሪ እንዲሆንና በሀገሪቷ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ግንባታ ላይ ያለውን ፋይዳ በመረዳት ጥራት ያለው የሰው ኃይል መረጃ በትምህርት ደረጃ፣ የሰው ኃይል ብዛት ለማወቅ፣ በየተቋማቱ ያሉትን ክፍት የስራ መደቦች ለመለየትና የተሟላ መረጃ ለማግኘት መሆኑን አንስተው ከዚህ ስራ የሚገኘው መረጃ መንግስት በመረጃና በማስረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ እንዲሰጥ ያግዛል ሲሉ ገልፀዋል። በተጨማሪም ኮሚሽነሩ ለዚህ ስራ መሳካት ድጋፍ ላደረጉ የክልል ቢሮ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶችና አመራሮች፣ በዚህ ስራ ለሚሳተፉ ባለሙያዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

a3a0928

በስልጠናው ከሀገሪቷ ዩኒቨርስቲዎችና ከቴክኒክና ሙያ ተቋማት የተውጣጡ መምህራንና ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በመረጃ መሰብሰብ ላይ ሲሰሩ የነበሩ ከ 4,000 በላይ ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

a3a0871
a3a0916