‘’የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነፃነት’’ በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ሀገራዊ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል

ግንቦት 10/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

702650666 1290096373307447 4716425942058237687 n

‘’የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነፃነት ‘’ በሚል በፕላንና ልማት ሚኒስቴርና በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በጋራ የተዘጋጀ ሀገራዊ ጉባኤ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ክቡር ዶ/ር ዐብይ አህመድን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።

702010308 967917672793455 7622087730413526352 n

መረጃ ሀገራዊ ራዕያችን የሆነውን ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት፣ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ዋነኛ ግብዓት መሆኑን አንስተው ይህን መረጃ በሀገር ባለሙያዎች ዕውቀትና ክህሎት በመሰብሰብ፣ በመተንተን በመረጃ ላይ የተመሰረተ ፖሊሲ ለማውጣትና ዕቅዶችን ለማቀድ ወሳኝ ግብዓት መሆኑን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ክቡር ዶ/ር ዐብይ አህመድ ገልፀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም የምናመነጫቸው የስታቲስቲክስ መረጃዎች መሬት ላይ ወርደው የማህበረሰቡ ህይወት ላይ ተጨባጭ የሆነ ለውጥ ማምጣት አለባቸው ሲሉ ገልፀዋል።

701273958 1292819229708196 528714209094895884 n

የዕለቱን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ፍፁም አሰፋ በሪፎርም ለውጡ ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ የስታቲስቲክስ መረጃ መሆኑን አንስተው ባለፉት ሶስት ዓመታት የስታቲስቲክስ ስትራቴጂክ ልማት ፕሮግራም በመቅረፅ ወሳኝ የሆኑ ጥናቶችና ቆጠራዎችን በማካሄድ ትላላቅ ስኬቶችና እመርታዎች መመዝገባቸውን ገልፀው፤ የሚገኙት መረጃዎችም ፖሊሲዎችን ለማውጣት፣ እቅድ ለማዘጋጀትና በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ለመስጠትን ዲጂታል ኢኮኖሚን እውን ለማድረግ ወሳኝ ነው ሲሉ ገልፀዋል።

702353881 1292818893041563 7848119583861261338 n

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ባለፉት ሶስት ዓመታት ባከናወናቸው ጥናቶችና ቆጠራዎች መረጃዎችን ለመሰበሰብ ሙሉ ለሙሉ የታብሌት ቴክኖሎጂ የተጠቀመ ሲሆን በተጨማሪም ዘመናዊ የጂ አይ ኤስ (GIS) ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የቆጠራ ቦታዎችን የማካለል ስራ፣ መረጃ ሰብሳቢዎች በተመደቡበት ቆጠራ ቦታ ላይ መገኘታቸውን በትራኪንግ ዘዴ ( tracking system) በመቆጣጠር፣ የሳተላይት ምልከታን ተጠቅሞ የግብርና ቆጠራን መረጃ በመሰብሰብ ጥራትና ወቅታዊነታቸውን የጠበቁ መረጃዎችን ለተጠቃሚዎች ለማቅረብ እየሰራ መሆኑ ተገልጿል።

701260395 1292819069708212 3041617130406295958 n
700014549 967917472793475 4239129991047166231 n

በጉባኤው ላይ በተዘጋጀው ኤግዚቢሽን ላይ በፕላንና ልማት ሚኒስቴርና በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የመረጃ መሰብሰብና ስርጭት ፕላትፎርሞች፣ የጂ አይ ኤስ (GIS) ቴክኖሎጂ፣ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎች ተጎብኝተዋል።

701558913 967920499459839 8587120512035772809 n 1
700669741 967917519460137 7126068212158298260 n
701227462 967917589460130 8342147434717322153 n
702995844 967917556126800 43424454000259241 n