ለተቋሙ የቀድሞ አመራር የሽኝት ፕሮግራም ተደረገ

ሐምሌ 5/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፣

1t8a2234.jpg

በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከጥቅምት 18/2015ዓ.ም እስከ ሰኔ 27/2017ዓ.ም ድረስ በኢኮኖሚ ስታቲስቲክስ  ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው ሲያገለግሉ ለቆዩትና ከሰኔ 25/2017ዓ.ም ጀምሮ በኢኖቬሽንና  ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ለተሾሙት አቶ ሙሉቀን ቀሬ በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት የሽኝት ፕሮግራም ተደረገ።

1t8a2672

በተቋሙ ከፍተኛ አመራርና ሠራተኞች በተዘጋጀ የሽኝት ፕሮግራም ላይ የተገኙት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር  ዴኤታ ክቡር  አቶ በረከት ፍስሀ ፅዮንና የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ክቡር አቶ ሙሉቀን ቀሬ በተቋሙ ቆይታቸው ለሰጡት የላቀ አመራርና ላሳዩት ትጋት ምስጋናቸውን አቅርበው ቀጣይ የስራ  ጊዜያቸው የተሳካ እንዲሆን ምኞታቸውን ገልፀዋል።

1t8a2688
1t8a2679
1t8a2800
1t8a2803